ሕግ መንግሥቱን በፖለሲ ማዕቀፍ ሥር?

ሰሞኑን በአንድ ካፌ ገብቼ የተደረደሩ ቀን ያለፈባቸው ጋዜጦች ስመለከት የሪፖርተር ጋዜጣ በሚያዚያ 1/2009 የእለተ-እሁድ እትሙ ላይ “ሰበር ሰሚ ችሎት  በክራውን ሆቴል የንግድ ምልክት ላይ የሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል ተባለ” በሚል ርእስ ባወጣው ዘገባ ላይ ዐይኔ አረፈ። ከዚህ በፊት በርካታ ጉዳዮች ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለመቅረባቸው አውቃለሁ። በሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ላይ የሕገ መንግሥት ጉዳይ ክርክር ተነስቶበት ወደ ጉባኤው ስለመቅረቡ ሳነብ ግን የመጀመሪያዬ ነው።  ምናልባት እኔ ያላወቅኳዋቸው ተመሳሳይ ጉዳዮች ከዚህ በፊት ቀርበው ይሆናል። ያም ሆነ ይህ ርእሰ ጉዳዩ ቀልቤን ስለሳበው ባለጉዳዮቹ  ስለተከራከሩበት ጉዳይና የችሎቱ ውሰኔ  ለማወቅ ጉጉት አደረብኝ። እናም  ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለተወሰደው የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔና ስለክርክሩ ከሥሩ ለማየት ወሰንኩ። ስለሆነም የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ቅጂ ፈልጌ በመመልከት የሚከተለውን  የግል እስተያየቴን ለመጻፍ ውደድኩኝ።

ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል የተባለው ውሳኔ ምንነት

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሰኔ የሰጠበት ጉዳይ በክራውን ሆቴል  ባለቤት (አመልካች) እና ሲክስ ኮንትኔታል ሆቴልስ (ተጠሪ) ከ2006 ዓ.ም ጀመሮ ከአእምሮ ንብረት ጽሕፈት እሰከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብሎም ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበ  ክርክር ነው። ይህ የመዝገብ ቁጥሩ 117013 የሆነውና ሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰኔ 22 ቀን 2008 በዋለውና አምስት ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተወሰነው ውሳኔ ከንግድ ምልክት ጥበቃ ጋር የተያየዘ ክርክር ነው። ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበው ጉዳይ ከንግድ ምልክት ምዝገባ  ተቃውሞ ጋር በተያየዘ የክራውን ሆቴል ባለቤት በአእምሮ ጽሕፈት ቤት ውሰኔ ቅር ተሰኝተው ለከፈተኛ ፍርድ ቤት ይገባኝ ያሉበት ጉዳይ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእእምሮ ጽሕፈት ቤት ውሳኔውን ስለኣጸና የፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ሲሆን፤ ሰበር ሰሚ ችሎቱም ጉዳዩን ከስር መሰረቱ በመፈተሽ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት ብሎ ለአመልካች ወስኗል። 

ጉዳዩ ከመሰረቱ ሲታይ በወርሃ ነሃሴ 2005 “CROWNE PLAZA” በሚል በተጠሪ በኩል  በቀረበው የንግድ ምልክት ምዝገባ ጥያቄ ላይ ተቃውሞ ካለ በቀረበው የጋዜጣ ጥሪ መሠረት አመልካች (CROWN HOTEL) በቃልና በጽሁፍ በተደጋጋሚ ተቃውሞ ያቀርባሉ። ለተቃውሞ ምክንያት የሆነው በሕግ ጠበቃ ያገኘውን የንግድ ምልክት የቀዳሚነት መብቴን ይጥሳል የሚል ነው። ተቃውሞው የተመሠረተው በአዋጅ 501/ 2005 አንቀጽ 6 እና  አንቀጽ 7 መሠረት ሲሆን በተለይም በአንቀጽ 7(1) “ከአንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይ እቃዎች ወይም አግልግሎቶች  ጋር የተያያዘ  የሌላ ሰው ቀዳሚ የንግድ ምልክት ጋር አንድ ዓይነት ወይም መሳከርን ሊያስከትል ተመሳሳይነት ያለው”  ሲሆን ለምዝጋባ በቁ አይደለም ብሎ በሚደነግገው መሠረት እንዲሁም በተጨማሪም በንግድ ምዝጋባ አዋጅ 686/2002 አንቀጽ 24 (3) (ሀ) መሠረት የንግድ መዝጋቢው አካል “ቀደም ሲል ከተመዘገቡት የንግድ ስሞች ጋር አንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይና አሳሳች አለመሆን  24 (3) (በ) መሠረት ደግሞ በንግድ ስም መዝገብ  በተመዘገበ የንግድ ስም ላይ ላይ ከፊቱ ወይም ከኋላው ቃላት በመጨመር ያልቀረበ መሆኑን በማረጋገጥ እንዲመዘገብ በሚደነግገው መሠረት ቀደም ሲል ተመዝግቦ ሥራ ላይ ካለው CROWN HOTEL+ logo ጋር ይመሳሰል። በዚህም በሕግ ጥበቃ ያገኘው መልካም ስሜና ዝናዬ ይነካል የሚል ነበር። እውነት ነው የእእመሮ ንብረት ጽሕፈት ቤት ትኩረት የንግድ ምልክቱ ወይም የፈጠራው ጉዳይ ላይ ሲሆን የንግድ መዝጋቢው አካል ደግሞ በንግድ ስሙ ላይ ያተኩራል። ቀዳሚነት ያለው የንግድ ምልክት “CROWN HOTEL” የሚል ሲሆን፤ አዲሱ የንግድ ምልክት “CROWNE PLAZA” የሚል ነው። የተጨመሩት ነገሮች በ CROWN ላይ” E”  እንዲሁም “PLAZA”  የሚለው ቃል ነው።  ሁሉቱም የሆቴል አግልግሎት ሰጪዎች መሆናቸው ልብ ይሏል። በክርከር ሂደቱ በርካታ ጭብጦት ለክርክር ቀርበው የነበረ ሲሆን የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በክርክር ሂደቱ በጭብጥነት ተይዞ እስከ መጨረሻ በዘለቀው  ጭብጥ ላይ ብቻ  የሚያተኵር ይሆናል። 

በፍርድ ሃተታው እንደተመለከተው በአመልካች በኩል ለተቃውሞ መነሻ የሆኑት የሕግ መሰረቶች  የንግድ ምዝገባ አዋጅ እና የንግድ ምልክት ምዝጋባ አዎጅ ሲሆኑ  ጽሕፈት ቤቱ በመጀመሪያ  ተቃውሞውን  ከአዋጅ 501/ 1998 ጋር በማገናዘብ ተቀበሎ የምዝገባ ሂደቱን አቋረጦ የነበረ ቢሆንም ለሁለተኛ ጊዜ ውሳኔውን ሊቀለበሰው ችሏል። ውሳኔው ለአመልካች ከተነገረ በኋላ እንደገና ውሰኔውን በመቀየር የሚከተሉት ምክንያቶችን አቅርቧል። ጽሕፈት ቤቱ የንግድ ምልክቶቹ መመሳሰል ሳይክድ ኢንቨስትመነትን ለማበረታት ይጠቅማል በሚል ሁለቱም የንግድ ምልክቶች እንዲቀጥሉ ወስኗል። አክሎም ጽሕፈት ቤቱ ውሳኔው እንዳይደገም ራሱን አስጠንቅቆ ዘግቶታል። ይህም ውሰኔው ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት ካለው ፍላጎት ውጭ ተገቢ እንዳለሆን ያመነበት ይመስላል። ምክንያቱ ይህንን ውሳኔ ከሰጠ በኋላ ተመሳሰይ ውሳኔ እንዳይደገም በራሱ ላይ እግድ አስቀምጧል። እዚህ ላይ ሊነሳ የሚቸለው ጥያቄ ውሳኔው ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እስከ ሆነ ድርስ የማይደገመበት ምክንያት ምንድ ነው? ከአዲሱ ድርጅት የተሻለ ኢንቨስትመነት ይዘው በተመሳሳይ  የንግድ ምልክት ለሚቀርቡ ባለሃብቶችስ ምን ዓይነት ምላሽ ሊስጥ ነው? ዜጎችን በእኩልና ፍታሃዊ መንገድ ሊያገልግል የቋቋመ ተቋም ልክ እንዳልሆነ አምኖ እንዳይደገም የሚለውን ውሳኔ እንዴት ሊወስን ይችላል? CRROWN HOTELS and Convention Center የሚል የንግድ ምልክት ይዞ ከቀደሙት ሁለቱ ሆቴሎች ይልቅ የተሻለ አቅም ያለው ባለሀብት ለምዝገባ ቢያመለክትስ? ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል።

Continue reading
  11813 Hits

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሕገ-መንግሥት መተርጎም ላይ ያለው ሚና እና በጉባዔው አዋጅ ላይ የተደረገ አጭር ምልከታ

 

መግቢያ

ሁሉም ሕጎች በራሳቸው ምሉዕ አይደሉም፡፡ በመሆኑም ሕጎችን በተገቢው የአተረጓጎም ሥርዓት መሠረት ተርጉሞ ሥራ ላይ ማዋል ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ደግሞ አጠቃላይ መርሆዎችን የደነገጉ ሕጎችን የያዙ እንደ ሕገ-መንግሥት ዓይነት ሕጎች በከፍተኛ ጥንቃቄ መሠረታዊ የአተረጓጎም መርሆዎችን በተከተለ ሁኔታ ፍጹም ገለልተኛና ብዘሀኑን በሚወክል ብቃት ባለው ሕገ-መንግሥት ተርጓሚ ሊተረጎም ይገባዋል፡፡ ይህም በመሆኑ ብዙ ሐገራት ሕገ-መንግሥት የሚተረጉም ራሱን የቻለ ተቋማትን አቋቁመዋል፡፡

ሐገራችን ኢትዮጵያም እንደሌሎች ሐገራት የሕገ-መንገስት ትርጉም ጥያቄ ሲቀርብ ጉዳዩን ተቀብሎ ተገቢውን ውሳኔ የሚሰጡ ተቋማትን አቋቁማለች፡፡ የኢ.ፊ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት የሕገ-መንግስታዊ ክርክር ጉዳይ ሲነሳ ጥያቄው እንዴት መልስ ያገኛል ለሚለው ድንጋጌ አስቀምጧል፡፡ በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 62 ላይ የፌደሬሽን ምክር ቤት ሕገ-መንግስቱን የመተርጎም ሥልጣን ይኖረዋል፡፡ የሕገ-መንግስታዊ ክርክር ጉዳይ ሲነሳ በፌደሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ያገኛል በማለት ደንግጓል፡፡ የፌደሬሽን ምክር ቤቱም የሕገ-መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ በሚያቀርብለት ሕገ- መንግስታዊ ጉዳይ ላይ በሠላሳ ቀናት ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል፡፡

የፌደሬሽን ምክር ቤት ሕገ-መንግስታዊ ትርጉም በሚሰጥበት ጊዜ ሞያዊ ዕገዛ የሚሰጠው የሕገ-መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሥልጣንና ተግባር በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 84 ላይ ተዘርዝሮ ተቀምጧል፡፡

Continue reading
  5677 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ሕገ-መንግሥት እና ፍርድ (ትርጉም)

 

 

 

መንደርደሪያ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስራ ዘመን ከማለቁ በፊት ምርጫን ማከናወን እንደማይችል፤ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ካሳወቀ ጊዜ ጀምሮ፤ የጉዳዩ ሕገ መንግሥታዊ ገፅታዎች በተለያዩ መድረኮች ውይይት እየተደረገባቸው ነው። አራት አማራጭ መፍትሄዎች የቀረቡለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ በጉዳዩ ላይ የሕገ መንግሥት ትርጉም፤ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጠይቋል። የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ፤ ጥያቄውን ተቀብሎ፤ የሕገ መንግሥት ምሁሮች አስተያየታቸውን በፅሁፍ እንዲያቀርቡ ጋብዟል። በቃልም እንዲያስረዱና ጥያቄዎችን እንዲያቀርቡ ጋብዟል።

የቀረበውን ግብዣ መሰረት በማድረግ አሰተያየት ለማቅረብ ውስኜ ነበር። በተለያዩ ምክንያቶች ሳላደርገው ቀርቻለሁ። አንደኛ፤ ግብዣው ለሕገ መንግሥት ምሁራኖች የቀረበ ጥሪ ነበር። ሁለተኛ፤ ጉባኤው የቀረበለትን አሰተያየት የመመልከት ግዴታ እንደሌለበት አስታውቋል። ሶስተኛ፤ በጊዜ እጥረት፤ በዛው ሳምንት የመጀመሪያ ልጄ ስለተወለደና በዚሁ ትኩረቴ ተይዞ የቆየ ስለነበረ። እንዲያም ሆኖ ግን በተለያዩ አጋጣሚዎች አንዳንድ አስተያየቶችን በማህበራዊ ሜዲያ ሳቀርብ ነበር። እነዚህን አስተያየቶቼን እንደሚከትለው አደራጅቼ አቅርቤያለሁ።

Continue reading
  7545 Hits

በፌዴሬሽን እና በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ም/ቤቶች የተሰጡ ውሳኔዎች ሕገ-መንግሥታዊነት

 

በዓለማችን እና በሀገራችን የተከሰተውን የኮቪድ-19 ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በሀገራችን የፌደራል መንግሥትና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች መታወጃቸው ተከትሎ የሀገራዊ ምርጫን መራዘምና ክልላዊ ምርጫ በትግራይ መከናወኑን ከሕገ-መንግሥቱ ድንጋጌዎች አኳያ እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡፡

በቅድሚያ ጥቂት በሆነችው ትልቅ ኢ-ሕገመንግሥታዊ ውሳኔን በመግለጽ ልጀምር፡፡ በሕገ-መንግሥታችን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊደነገግ የሚገባው በሁለት ምክንያቶች ማለትም፡-

1ኛ/ በሰው ሰራሽ አደጋ (የውጪ ወረራ ሲከሰት እና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥል ሁኔታ ሲከሰት)

2ኛ/ በተፈጥሮ አደጋ (ጎርፍ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የህዝብ ጤንነትን አደጋ ላይ የሚጥቅ ሁኔታ ሲከሰት) ስለመሆኑ የፌደራሉ ሕገ-መንግሥት አ.ቁ 93(1) የሚደነግግ ሲሆን በ2ኛው የተፈጥሮ አዳጋ ሲከሰት የፌደራል መንግሥቱ ብቻ ሳይሆን ክልላዊ መንግሥቶች አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የማውጣት ሥልጣን ይኄው የሕግ መንግሥት አንቀጽ 93(1)(ለ) መብትን ይሰጣቸዋል፡፡ በመሆኑም የሀገራችን የበላይ ሕግ የሆነው አካል ለሁለቱም መንግሥታት እኩል ሥልጣን በሰጠው ጉዳይ ላይ የአንደኛው ከአንደኛው የሚበልጥበት ወይም አንደኛው በአንደኛው ላይ የበላይ የሚሆንበት ሁናቴ የለም፡፡ ነገር ግን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት መጋቢት 30 ቀን 2012 ዓ.ም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ ያወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በክልሎች ከሚወጡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች ሁሉ የበላይ ስለመሆኑ መደንገጉ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ነው፡፡

Continue reading
  3683 Hits

የሕገ-መንግሥት ፍርድ ቤት፡ የብሔርና ብሔረሰቦች ሉዓላዊነት መቃብር

 

 

በሀገራችን ህዝባዊ አመጽን ተከትሎ በሰኔ 2010 ዓ.ም ብትረ መንግሥቱን የሚዘውረው የብልጽግና ፓርቲ ለአመጹ ምክንያት የሆኑትን የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ የተቋም ግንባታ እና የህግ ለውጦችን እያደረገ ነው፡፡

በተጨማሪም ገዢው የብልጽግና ፓርቲ ከኦሮሚያ እና አማራ ብሔር ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመሆን በቅርቡ በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ሕገ-መንግሥቱን በጋራ እንዲሻሻል ለማድረግ የሚሰሩ ስለመሆኑ ተፈራርመዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲሚሻሻሉ በጋራ የተስማሙባቸው የሕገ-መንግሥት የአንቀጾች ዝርዝር ላይ ስምምነት ላይ አልደረሱም(ወይም ለህዝብ ሊገልጹት አልፈለጉም)፡፡ ነገር ግን በመግባቢያው ሰነድ ላይ ከፈረሙት አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከጥቂት የሕገ-መንግሥት ምሁራን እንዲሻሻል ጥያቄ የሚቀርብበት አንዱ ድንጋጌ የሕገ-መንግሥት አንቀጽ 62(1) የሆነውና “ሕገ-መንግሥትን የመተርጓም” እና በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣንን ከምክር ቤቱ ተወስዶ የሕገ-መንግሥት ጉዳይን የሚያይና የሚወስን የሕገ-መንግሥት ፍ/ቤት እንዲቋቋም በማለት ባህር አቋርጠው የምዕራቡንና የምስራቁም ልምድ በማስረጃነት በመጥቀስ በሀገራችንም ይህ ተግባራዊ እንዲሆን እየሞገቱ ይገኛሉ፡፡

Continue reading
  3153 Hits

Constitutionality of Constitutional Interpretation Uncontestable

In his viewpoint article headlined, “Unconstitutional Declaration of Unconstitutionality” (Volume 14, Number 719, February 9, 2014) posted at addis fortune, Mulugeta Argawi argued that the latest constitutional interpretation of Melaku Fenta’s case is unconstitutional, in and of itself. His argument rests on Article 84 (2) of the Constitution. I believe that it is important to counter his argument by focusing on the laws themselves.

Mulugeta’s criticism rotates around the purely legalistic thinking that a court of law cannot entertain any constitutional matter until such a time that either of the parties raise the issue, which should, in turn, be disputed and contested by the other.

But this is true only in a civil suit. It does not hold water in issues of constitutional interpretation.

Constitutional interpretation is not about litigation or jurisdiction. It is all about maintaining constitutionalism. Of course, there are varying mechanisms of interpreting constitutions, but even then, courts do not follow civil procedures.

Let us take the US constitutional tradition, for example. Even though all courts have parallel power to review and decide on issues of constitutionality, there should not necessarily be two litigants fighting for a case. Many cases have been raised as issues of constitutional rights (and hence constitutional interpretations), which were not exactly cases of one party against the other.

Continue reading
  10321 Hits

ሕገ መንግሥታዊ የዋስትና መብትን በመተርጎም በኩል ስለታየው ችግር

 

መግቢያ

ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን ስምምነት& ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሕግጋት እና በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የተካተቱት ሥነ ሥርዓታዊ መብቶች መሠረታዊ ዓላማ መርማሪ አካላት ያለበቂ ምክንያትና ሕጋዊ ሥርዓት የአንድን ሰው የነጻነት መብት እንዳይጥሱ ዋስትና እና ጥበቃ መስጠት ነው፡፡ የብዙ አገሮች ሕገ መንግሥት የአንድ ሰው በሕይወት የመኖር& የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት ከሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክቡርነት የመነጩ ሊደፈሩና ሊገሰሱ የማይችሉ መብቶች መሆናቸውን ያረጋገጣሉ@ መሠረታዊ መብቶቹ ተግባር ላይ እንዲውሉ ጥረት የሚደረግ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ በሌላ በኩል የእነዚህን መብቶች አፈፃፀም የሚሸረሽሩ ወይም ዋጋ የሚያሳጡ የተለያዩ የወንጀል ድርጌቶች በዓለም ውስጥ በየደረጃው በስፋት ሲፈፀም ማየትና መስማት የተለመደ ሆኗል፡፡ ይህ የማይጣጣም ሁኔታ ከልዩ ልዩ የጥቅም ግጭቶች& ከአመለካከት ልዩነት& ካለመቻቻልና ከመሣሰሉት መንስዔዎች የሚመነጭ ሊሆን ይችላል፡፡

በዓለም አቀፍ ሆነ በብሔራዊ ሕግጋት ዕውቅና ከተሰጣቸው መሠረታዊ መብቶች አንዱ በወንጀል የተከሰሰ ሰው ጉዳዩ ሥልጣን ባለው ፍርድ ቤት ታይቶ ጥፋተኛ መሆኑ እስካልተረጋገጠ ድረስ ከወንጀል ነፃ እንደሆነ የመቆጠር መብት ያለው መሆኑ ነው፡፡ ይህ መሠረታዊ መብት ዕውቅና ሊያገኝ የቻለው ንፁሀን ግለሰቦች በወንጀል በመጠርጠራቸው ወይም በመከሰሳቸው ብቻ ሊደርስባቸው የሚችለውን የተለያየ የመብት ጥሰት ለመግታት ነው፡፡

ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ የተያዘ ሰው በመሠረቱ የተጠረጠረበት ወንጀል በማስረጃ ከተረጋገጠበት ሊፈረድበት@ ማስረጃ ከሌለ ግን ሊፈታ ይገባል፡፡ ሆኖም መረማሪ ፖሊስ ወይም ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩን እስኪያጣሩና ለፍርድ እስኪቀርብ ድረስ ታሣሪው በጥፋተኝነት የማይቀጣበት ወይም በፍጹም ነፃነት የማይለቀቅበት ሁኔታ አለ፡፡ ይህም በዋስ የመለቀቅ መብት ነው፡፡ መንግሥት የሕብረተሰብን ሰላምና ፀጥታ የማስከበር እንዲሁም የግለሰብን መብትና ነፃነት የማክበር ሃላፊነት አለበት፡፡ መንግሥት የወንጀል ተግባር ፈጽመዋል በማለት በሚይዛቸው ሰዎች ላይ ሕግ ለማስከበር የሚፈጽመው ተግባር ሁለት ተፋላሚ የሆኑ ጥቅሞችን የሚያስታርቅና የሚያቻችል መሆን አለበት፡፡ የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ሲባል በከባድ የወንጀል ተግባር የተጠረጠሩ ሰዎችን በፍርድ አደባባይ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ለማድረግ  ከፍርድ በፊት ማሰሩ ተገቢ ሲሆን በሌላ በኩል ተጠርጠረው የታሰሩ ሰዎች ንፁህ ሰዎች የሚሆኑበት እድል ሰፊ ስለሆነ ከፍርድ በፊት እንዳይታሰሩ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡  

Continue reading
  14174 Hits

የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ጥያቄና ሕገ መንግሥቱ

 

መግቢያ

የማንነት ጥያቄ ምንድን ነው? የድንበር አከላለል ለውጥ (የድንበር ውዝግብ) ጥያቄስ ምንድን ነው? የኢትዮጵያ ሕግስ እንዴት ነው የሚጠብቃቸው? የዚህ ማስታወሻ ዓላማ እነዚህን ጉዳዩች ስለሚመለከቱት የሕግ ክፍሎች በማጥናትና ስለአተረጎማቸው አስተያየት በማቅረብ እነዚህን ጥያቄዎች መመለስ ነው፡፡ ከእነዚህ ባሻገር ይህ ማስታወሻ ስለ ትግራይ ሕዝብ መልክዓ ምድራዊ አሰፋፈር ታሪካዊ ዳሰሳ ባጭሩ አድርል፡፡

ይህን ማስታወሻ ለመጻፍ ያነሳሱኝ ነገሮች የፌዴሬሽን ምክር ቤት የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ ተወካዮች በቀረበለት በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀጽ 20 ድንጋጌ መሠረት የማንነት ጥያቄው በክልሉ በደረጃው ባሉ የአሰተዳደር እርከኖች ታይቶ ውሳኔ ማግኘት የሚገባው በመሆኑ ጉዳዩ በትግራይ ክልል እንዲታይ ብሎ በመወስን ማስተላለፉ እና የእኔ ማንነት ናቸው፡፡ በዚህ የተነሳ ዋናው ጥያቄ  የሆነውን የማንነት ጥያቄ ምንነትና የድንበር አከላለል ለውጥ (የድንበር ውዝግብ) ጥያቄ ምንነት በመመርመር ስለአተረጎገማቸው አስተያየት ማቅረብ ወደድኩኝ፡፡

1.    የማንነት ጥያቄ ባሕርይ ጥያቄውን የማቅረብ መብት    

Continue reading
  13800 Hits