ሕግ መንግሥቱን በፖለሲ ማዕቀፍ ሥር?

ሰሞኑን በአንድ ካፌ ገብቼ የተደረደሩ ቀን ያለፈባቸው ጋዜጦች ስመለከት የሪፖርተር ጋዜጣ በሚያዚያ 1/2009 የእለተ-እሁድ እትሙ ላይ “ሰበር ሰሚ ችሎት  በክራውን ሆቴል የንግድ ምልክት ላይ የሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል ተባለ” በሚል ርእስ ባወጣው ዘገባ ላይ ዐይኔ አረፈ። ከዚህ በፊት በርካታ ጉዳዮች ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለመቅረባቸው አውቃለሁ። በሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ላይ የሕገ መንግሥት ጉዳይ ክርክር ተነስቶበት ወደ ጉባኤው ስለመቅረቡ ሳነብ ግን የመጀመሪያዬ ነው።  ምናልባት እኔ ያላወቅኳዋቸው ተመሳሳይ ጉዳዮች ከዚህ በፊት ቀርበው ይሆናል። ያም ሆነ ይህ ርእሰ ጉዳዩ ቀልቤን ስለሳበው ባለጉዳዮቹ  ስለተከራከሩበት ጉዳይና የችሎቱ ውሰኔ  ለማወቅ ጉጉት አደረብኝ። እናም  ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለተወሰደው የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔና ስለክርክሩ ከሥሩ ለማየት ወሰንኩ። ስለሆነም የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ቅጂ ፈልጌ በመመልከት የሚከተለውን  የግል እስተያየቴን ለመጻፍ ውደድኩኝ።

  15223 Hits

የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ጥያቄና ሕገ መንግሥቱ

የማንነት ጥያቄ ምንድን ነው? የድንበር አከላለል ለውጥ (የድንበር ውዝግብ) ጥያቄስ ምንድን ነው? የኢትዮጵያ ሕግስ እንዴት ነው የሚጠብቃቸው? የዚህ ማስታወሻ ዓላማ እነዚህን ጉዳዩች ስለሚመለከቱት የሕግ ክፍሎች በማጥናትና ስለአተረጓጎማቸው አስተያየት በማቅረብ እነዚህን ጥያቄዎች መመለስ ነው፡፡ ከእነዚህ ባሻገር ይህ ማስታወሻ ስለ ትግራይ ሕዝብ መልክዓ ምድራዊ አሰፋፈር ታሪካዊ ዳሰሳ ባጭሩ አድርጓል፡፡

  17593 Hits

Constitutionality of Constitutional Interpretation Uncontestable

In his viewpoint article headlined, “Unconstitutional Declaration of Unconstitutionality” (Volume 14, Number 719, February 9, 2014) posted at addis fortune, Mulugeta Argawi argued that the latest constitutional interpretation of Melaku Fenta’s case is unconstitutional, in and of itself. His argument rests on Article 84 (2) of the Constitution. I believe that it is important to counter his argument by focusing on the laws themselves.

  13458 Hits

ሕገ መንግሥታዊ የዋስትና መብትን በመተርጎም በኩል ስለታየው ችግር

ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን ስምምነት& ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሕግጋት እና በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የተካተቱት ሥነ ሥርዓታዊ መብቶች መሠረታዊ ዓላማ መርማሪ አካላት ያለበቂ ምክንያትና ሕጋዊ ሥርዓት የአንድን ሰው የነጻነት መብት እንዳይጥሱ ዋስትና እና ጥበቃ መስጠት ነው፡፡ የብዙ አገሮች ሕገ መንግሥት የአንድ ሰው በሕይወት የመኖር& የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት ከሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክቡርነት የመነጩ ሊደፈሩና ሊገሰሱ የማይችሉ መብቶች መሆናቸውን ያረጋገጣሉ@ መሠረታዊ መብቶቹ ተግባር ላይ እንዲውሉ ጥረት የሚደረግ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ በሌላ በኩል የእነዚህን መብቶች አፈፃፀም የሚሸረሽሩ ወይም ዋጋ የሚያሳጡ የተለያዩ የወንጀል ድርጌቶች በዓለም ውስጥ በየደረጃው በስፋት ሲፈፀም ማየትና መስማት የተለመደ ሆኗል፡፡ ይህ የማይጣጣም ሁኔታ ከልዩ ልዩ የጥቅም ግጭቶች& ከአመለካከት ልዩነት& ካለመቻቻልና ከመሣሰሉት መንስዔዎች የሚመነጭ ሊሆን ይችላል፡፡

  18045 Hits

የሕገ-መንግሥት ፍርድ ቤት፡ የብሔርና ብሔረሰቦች ሉዓላዊነት መቃብር

በሀገራችን ህዝባዊ አመጽን ተከትሎ በሰኔ 2010 ዓ.ም ብትረ መንግሥቱን የሚዘውረው የብልጽግና ፓርቲ ለአመጹ ምክንያት የሆኑትን የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ የተቋም ግንባታ እና የህግ ለውጦችን እያደረገ ነው፡፡ በተጨማሪም ገዢው የብልጽግና ፓርቲ ከኦሮሚያ እና አማራ ብሔር ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመሆን በቅርቡ በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ሕገ-መንግሥቱን በጋራ እንዲሻሻል ለማድረግ የሚሰሩ ስለመሆኑ ተፈራርመዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲሚሻሻሉ በጋራ የተስማሙባቸው የሕገ-መንግሥት የአንቀጾች ዝርዝር ላይ ስምምነት ላይ አልደረሱም(ወይም ለህዝብ ሊገልጹት አልፈለጉም)፡፡

  6325 Hits

በፌዴሬሽን እና በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ም/ቤቶች የተሰጡ ውሳኔዎች ሕገ-መንግሥታዊነት

በዓለማችን እና በሀገራችን የተከሰተውን የኮቪድ-19 ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በሀገራችን የፌደራል መንግሥትና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች መታወጃቸው ተከትሎ የሀገራዊ ምርጫን መራዘምና ክልላዊ ምርጫ በትግራይ መከናወኑን ከሕገ-መንግሥቱ ድንጋጌዎች አኳያ እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡፡

  6723 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ሕገ-መንግሥት እና ፍርድ (ትርጉም)

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስራ ዘመን ከማለቁ በፊት ምርጫን ማከናወን እንደማይችል፤ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ካሳወቀ ጊዜ ጀምሮ፤ የጉዳዩ ሕገ መንግሥታዊ ገፅታዎች በተለያዩ መድረኮች ውይይት እየተደረገባቸው ነው። አራት አማራጭ መፍትሄዎች የቀረቡለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ በጉዳዩ ላይ የሕገ መንግሥት ትርጉም፤ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጠይቋል። የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ፤ ጥያቄውን ተቀብሎ፤ የሕገ መንግሥት ምሁሮች አስተያየታቸውን በፅሁፍ እንዲያቀርቡ ጋብዟል። በቃልም እንዲያስረዱና ጥያቄዎችን እንዲያቀርቡ ጋብዟል።

  11231 Hits

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሕገ-መንግሥት መተርጎም ላይ ያለው ሚና እና በጉባዔው አዋጅ ላይ የተደረገ አጭር ምልከታ

ሁሉም ሕጎች በራሳቸው ምሉዕ አይደሉም፡፡ በመሆኑም ሕጎችን በተገቢው የአተረጓጎም ሥርዓት መሠረት ተርጉሞ ሥራ ላይ ማዋል ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ደግሞ አጠቃላይ መርሆዎችን የደነገጉ ሕጎችን የያዙ እንደ ሕገ-መንግሥት ዓይነት ሕጎች በከፍተኛ ጥንቃቄ መሠረታዊ የአተረጓጎም መርሆዎችን በተከተለ ሁኔታ ፍጹም ገለልተኛና ብዘሀኑን በሚወክል ብቃት ባለው ሕገ-መንግሥት ተርጓሚ ሊተረጎም ይገባዋል፡፡ ይህም በመሆኑ ብዙ ሐገራት ሕገ-መንግሥት የሚተረጉም ራሱን የቻለ ተቋማትን አቋቁመዋል፡፡

  8953 Hits