ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት (የግዴታ ሥራ) እንደ ወንጀል ቅጣት

ጣልያንን ለዘጠኝ ዓመታት የመሩት የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ ፕሬዚዳንትና ባለቤት እንዲሁም ቢሊየነሩ ሲልቪዮ ቤርሎስኮኒ በተከሰሱበት የታክስ ማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሚላን ከተማ የሚገኘው ፍርድ ቤት ቤርሎስኮኒ የአራት ዓመታት እስራት ቢፈረድባቸውም የእስራት ቅጣቱ በተለያዩ ምክንያቶች ቀርቶ በተቃራኒው ቤርሎስኮኒ በአረጋውያን ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል ውስጥ ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ እ.ኤ.አ. በ2013 መወሰኑ ይታወቃል፡፡ በውሳኔው መሠረትም ቤርሎስኮኒ ሴሴኖ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና ከ2000 በላይ በእድሜያቸው የገፉ፣ የአእምሮና የአካል ጉዳተኛ የሆኑ አረጋውያን በሚገኙበት ማዕከል ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል በሳምንት ለአራት ሠዓታት በማዕከሉ እየተገኙ አረጋውያኑን እንዲመግቡ፣ እንዲንከባከቡ፣ እንዲያንሸራሽሩ እንደ አጠቃላይም በማንኛውም መልኩ ከአረጋውያኑ ጎን እንዲሆኑ ተወስኖባቸው ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱን ፈፅመው አጠናቀዋል፡፡

  18455 Hits