የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ማቆም መብትና ሕገወጥ ተግባሮች ምንነት በኢትዮጵያ የሕግ ማዕቀፍ

 

የዚህ አጭር ጽሑፍ ዓላማ የሲቪል አቪዬሽን ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማና የፌዴራል ፖሊስ የእስር ዕርምጃ ተከትሎ በተለያዩ ሚዲያዎች በመንግሥት በኩል በተወሰዱት ዕርምጃዎች ዙሪያ እየቀረቡ ያሉ ሕግ ነክ አስተያየቶች ውይይቶች፣ ሰሞነኛ ክርክሮችንና ተያያዥ ነጥቦች መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ውስጥ የመንግሥት ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ ማቆም መብት የሕግ ወሰን እስከ የት ድረስ ነው? የሚለውን ጥያቄ ከሕገ መንግሥት መሠረታዊ መርሆች አንፃር በመመልከት በመብቱ አፈጻጸም ላይ የሚነሱ አንዳንድ የሕግ ጉዳዮችን በአጠቃላይ በአገሪቱ የተለያዩ የአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታዎችን አስመልክቶ በፌዴራል መንግሥት በኩል ከወጡ ሕጎች አንፃር በመጠኑ መዳሰስ ነው፡፡

የሥራ ማቆም መብት ጽንሰ ሐሳብና በሕግ የተሰጠው ጥበቃ

የሥራ ማቆም አድማ ሠራተኞች በሕግ ዕውቅና ተሰጥቶት ያለ የኅብረትና በነፃነት የመደራጀት ሰፊ የሆነው መሠረታዊ መብት አንዱና ወሳኝ ከሚባሉት ውስጥ የሚጠቀስ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የሥራ ማቆም ዕርምጃ ሠራተኞች ለአንድ የተወሰነ ወቅት የሚሠሩትን ሥራ እንዲቋረጥ በማድረግ ለጋራ ፍላጎታቸው በአንድነት በመሆን አቋማቸውን የሚገልጹበት የመታገያ ሥልት ነው፡፡ በአጠቃላይ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ ሁኔታ ከሥራቸው ጋር በቀጥታ በሚገናኙ ማንኛውም ጉዳዮች በተለይም ደግሞ ከተቋማዊ፣ ከማኅበራዊና ከኢኮኖሚያዊ በቀጥታ በሚያያዙ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ጥያቄያቸውን ሕጉን ተከትለው ለሚመለከታቸው መንግሥታዊ ውሳኔ ሰጪ አካላት የሚያቀርቡበትና ድምፃቸውን ለማሰማት የሚችሉበት የመደራደሪያ ሕጋዊ ሥልቶች ነፀብራቅ እንደሆነ ከሠራዊቶች የቡድን መብቶች ታሪካዊ አመጣጥና ከዳበሩት የሕግ ፍልስፍናዎች የተጻፉ ዓለም አቀፍ የሕግ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ይህም ሲባል መብትና ጥቅማቸውን አንድም በሚመሠርቱት የሠራተኛ ማኅበሮች በኩል ወይም በጋራ በመሆን አሠሪዎቻቸው ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር የሚያስችላቸው ሕጋዊ መንገድ እንደሆነ ዓለም አቀፍ የሠራተኞች መብትን ለማስጠበቅ ከወጡ ስምምነቶች መገንዘብ ይቻላል።

 የዓለም አቀፉን የሠራተኞች መብት በሕግ ጥበቃ ለማሰጠት ከወጡት የተለያዩ ስምምነቶች እንዲሁም አገሮች አባል የሆኑበት የበላይ ጠባቂ የሆነው ተቋም (International Labor Organization (ILO)) አማካይነት በየጊዜው ስለሠራተኞች በነፃነት የመደራጀትና የሠራተኛ ማኅበራት የመመሥረት መብት (Right to Organize & Collective Bargaining Convention (1948/51)) & Freedom of Association & Protection of the Right to Organize Convention) (1948/51)) አስመልክቶ በዝርዝር ከፀደቁት የሕግ ሰነዶች እያንዳንዱ አገሮች በውስጥ የሕግ ማዕቅፎቻቸው ተጨባጭ ሁኔታዎቻቸውን መሠረት በማድረግ ለመብቱ አፈጻጸምና አተገባበር ልዩ ሕጎች በማውጣት ሕጋዊ ጥበቃና ምቹ ሁኔታዎችን እንዲፈጥሩ ግዴታዎችን ያስቀምጣሉ፡፡   በተለይም ኢትዮጵያ አባል የሆነችበትና በ1987 ዓ.ም. በፀደቀው የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ምዕራፍ 3 አካል የሆነው የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ መብቶችን ለመደንገግ የወጣው የቃል ኪዳን ሰምምነት (International Convenant on Economic, Social, and Cultural Rights (ICESCR)) የሠራተኞች አጠቃላይ መብቶችን በሚመለከት ልዩ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ከመሆኑም በተጨማሪ በቃል ኪዳን ስምምነት ሰነዱ አንቀጽ 8 ውስጥ የሥራ ማቆም ዕርምጃ የመውሰድ መብት የየአገሮቹን ገዥ ሕጎች ተከትሎ በሁሉም መስክ የሚገኙ ሠራተኞች ገደብ ሊጣልባቸው ከሚችሉት ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከፖሊስና ከመንግሥት የአስተዳደር ሠራተኞች በስተቀር መብቱ ሳይሸራረፍና ያለአድልኦ በእኩልነት ሊከበር እንደሚገባው ዋስትና ይሰጣል፡፡ ሆኖም አባል አገሮች በውስጥ ባላቸው ተጨባጭ ሁኔታዎች አንፃር በማገናዘብ በሕጎቻቸው ላይ የተወሰኑ ገደቦች እንዲሁም የሥራ ማቆም ዕርምጃ ፈጽሞ ማድረግ የማይቻልባቸውን ዘርፎች በሚመለከት በዝርዝር ሕግ መከልከል እንደሚችሉ ነገር ግን የሠራተኞች የጋራ መብት ፍፁምነት የሌለው ቢሆንም፣ እንኳን ገደብም ሆነ ክልከላ ለማድረግ የሚቻለው ቢያንስ ቢያንስ ግልጽ የሆኑትን ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያገኙ ሕጋዊ መሥፈርቶችንና አሠራሮች ጋር ተጣጥሞና መሠረታዊ የሆነውን የመብቱን ዓላማ በማይቃረን መልኩ ሊሆን እንደሚገባ ያስረዳሉ፡፡

Continue reading
  11855 Hits

የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ መቁረጥ እና ሕጋዊነቱ

 

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው ገበታ ለሃገር መርሃግብር የመንግሥት ሠራተኞች የወር ደሞዛቸውን ለገሱ የምትል ዜና በተደጋጋሚ በመስማቴ እና እውነት በዚህ የኑሮ ውድነት እነዚህ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዛቸውን የሚለግሱት ጎርጎራ፣ ወንጪ አሊያም ኮይሻ  ላይ ሆቴል መሰራቱ ከጊዚያዊ ችግሮቻችን ይበልጣል ብለው አምነው ወይስ በአለቆቻቸው ተፅዕኖ ሥር በመሆናቸው ተገድደው የሚለው ጥያቄ በተደጋጋሚ ውስጤ ሲመላለስ በመቆየቱ ነው፡፡ መልካም ንባብ!

ለጠቅላይ ሚኒስትራችን ምስጋና ይግባቸውና አይነ-ግቡ የሆኑ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከቤተ-መንግሥታቸው ጀምረው እየገነቡልን ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ስራዎች የሃገርን ገፅታ ከመገንባት ጀምሮ ታሪክን ጠብቆ በማቆየት በቱሪዝም እንደሃገር የሚገኘው ገቢ ከፍተኛ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ትልቅ ተስፋ የተጣለባቸው መሆናቸው በስፋት ይጠቀሳል ይሁን እንጂ በተቃራኒው ቅንጦት ነው፣ በዚህ ሰዓት ሰላም እና በልቶ ማደር እንጂ ቅንጡ ሆቴል የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ ከቁጥር አይገባም ስለሆነም ያለጊዜው የመጣ ፕሮጀክት ነው በማለት የሚተቹትም አልጠፉም፡፡

ቤተመንግሥትን ከማስዋብ የተጀመረው ፕሮጀክት አሁን አድማሱን አስፍቶ ሃገራዊ ቅርፅን በመላበስ በሶስት ክልሎች ማለትም አማራ፣ ኦሮሚያ እና ደቡብ ያሉ የመስህብ ስፍራዎችን ወደማልማት ተሸጋግሯል፡፡ ለዚህም እውን መሆን ገበታ ለሃገር በሚል በገቢ ማሰባሰቢያ መልክ የ10,000,000 ብር እና 5,000,000 ብር የሚከፈልበት እራት ግብዣ በጠቅላያችን ተሰናድቷል፡፡ በዚህ አላበቃም በኢትዮ ቴሌኮም አማካኝነት ዜጋው ልቡ በፈቀደ መጠን ገንዘብ እንዲለግስ አጭር የጽሑፍ መልዕክት ተዘጋጅቷል፤ የባንክ አካውንትም በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ በማድረግ ገቢ ማሰባሰብ ስራው ቀጥሏል፡፡ ይሁን እንጂ ፕሮጀክቱ ይፋ ሲደረግ ያልተገለፀ ነገር ግን በተግባር እየሆነ ያለ አንድ እውነት አለ፡፡ ይህም የመንግሥት ሠራተኛው ለፕሮጀክቱ የወር ደሞዙን እንዲሰጥ ማድረግ፡፡ የእንትን ሚኒስቴር ሠራተኞች እና አመራሮች ለገበታ ለሃገር የወር ደሞዛቸውን ለገሱ የሚል ዜና በየዕለቱ እየሰማን ነው፡፡ ለመሆኑ የሠራተኛ ደመወዝ የሚቆረጠው እንዴት ነው?፣ አንድ የስራ ሃላፊ ስለፈለገ ወይም መስሪያቤቱ አመራሮች ተወያይተው ስላፀደቆ የሠራተኛን ደመወዝ መቁረጥ ይቻላል እንዲቆረጥብን አንፈልግም የሚሉ ሠራተኞች ሲኖሩ እንዴት ይደረጋል?፣ የሚሉ ጥያቄዎች በዚህ ጽሑፍ መልስ ለመስጠት ይሞከራል፡፡

 

Continue reading
  10964 Hits