የሰበር ፍርድ ያለማክበር ልማድና ውጤቱ

ጸሐፊው በሚከታተለው አንድ የንግድ ችሎት ጉዳይ ጠበቃው የችሎቱን ዳኛ ያማርራል፡፡ የዳኛውን የችሎት አካሄድ እየተቸ በዕለቱ በሰጠው ፍርድ ጠበቃው ለጉዳዩ ጠቃሚ የሆነውን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ የሕግ ትርጉም የችሎቱ ዳኛ በፍርዱ አለማካተቱ፣ ለጉዳዩ አግባብነት ያለው መሆኑንና ይዘቱንም በፍርዱ ለማንፀባረቅ ፈቃደኛ አለመሆኑ እጅጉን አንገብግቦታል፡፡ እንደ ጠበቃው አነጋገር ‹‹ከሳሾች ባቀረቡት ክስ ለጉዳዩ አግባብነት ያለውን የሰበር ችሎት ቅጹን፣ የመዝገብ ቁጥሩንና ቀኑን አመልክተን አቀረብን፣ በቃል ክርክርም ይህንኑ በአጽንአት እንዲመዘገብልን አመለከትን፤›› ይላል፡፡ ውጤቱን ሲገልጽ ደግሞ ዳኛው በፍርዱ ሀተታውም ሆነ ትንታኔ የሰበር ችሎቱን ፍርድ አልገለጸም፣ የሰጠውም ፍርድ ሰበር ችሎቱ ከሰጠው አስገዳጅ ትርጓሜ ጋር የሚጋጭ በመሆኑ በይግባኝ ከማሳረም ውጭ አማራጭ እንደሌለው ተናገረ፡፡ 

  10746 Hits

ጠበቃ በጋብቻ ፍቺ ሂደት ስለሚኖረው የሙያ ወሰን እና የሰበር ተቃርኖ

ጋብቻ በሁሉም ባህሎችና ሃይማኖቶች ትልቅ ክብር እና ልዩ ቦታ የሚሰጠው የሃገር ምሶሶ የሆነ የቤተሰብ ተቋም የሚፈጥ ሕጋዊ ኩነት ነው፡፡ በመሆኑም ፀንቶ እንዲቆይ በመንግስት እና በህብረተሰቡ ጥበቃ ይደረግለታል፡፡ መንግስት ጋብቻ ሲመሰረት፣ በጋብቻ ውስጥ እና ሲፈርስ ግንኙነቱ የሚመራበትን ሥነ ስርዓት በህግ በመደንገግ ጥበቃ ያደርጋል፡፡ ጋብቻ በፍች እንዲፈርስ ጥያቄ በሚቀርብበት ወቅት ፍርድ ቤት ጋብቻው ፀንቶ እንዲቆይ ለማስቻል ሊከተላቸው እና ሊፈፀማቸው የሚገቡ የጥበቃ ሥነ-ሥርዓት በቤተሰብ ህግ ተደንግጓል፡፡ (አንቀፅ 76 - 82 ይመለከቷል)። 

  2679 Hits

የሰበር ዓላማ ወጥነትን ማስፈን ወይስ ሕገ-ወጥነትን ማስፋፋት?

ጊዜው እ.ኤ.አ 1954 ነው፡፡ ለአለም ሀገራት የዲሞክራሲ አርአያና መምህር ነኝ ብላ በምትደሰኩር በአሜሪካ ሀገር ነጭና ጥቁር ተማሪ በአንድ ላይ አይማርም ነበር አሉ፤ ምክንያቱም ጥቁር ተማሪ ከነጭ ተማሪ ጋር በአንድ ላይ እንዲማር መፍቀድ ማለት በነጭ ተማሪዎች ሞራልና ክብር መቀለድ ነው ብላ ታምን ነበር፤ አሜሪካ፡፡ በመሆኑም ጥቁሮችና ነጮች ተለያይተው ይማሩ ነበር ማለት ነው፡፡ በዚሁ አይን ያወጣ አድልዎ የተበሳጨው ብራውን የተባለው ግለሰብ በአሜሪካ ሀገር የካንሳስ ክልል የትምህርት ጉዳይ ቦርድን በፍርድ ቤት ገተረው፡፡ ሚስተር ብራውን ለጥቁሮች ሽንጡን ገትሮ ከተከራከረ በኃላ ጥቁሮችን አንገት የሚያቀና ፍርድ አስፈረደ፡፡ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጥቁርና ነጭ ተማሪዎች ተለያይተው እንዲማሩ ማድረግ የሰው ልጆች በተፈጥሮ እኩል ሆኖው የመፈጠር መብትን የሚቃረን በተለይም ደግሞ የጥቁሮች ክብርና ሞራል የሚነካ እኩል የትምህርት እድል የሚነፍግ ህገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ ከተፈጥሮ ሕግና የአሜሪካ ህገ መንግስት ጋር የሚጣረስ ነው ሲል ለሰው ልጆች እኩልነት የሚያረጋግጥ ፍርድ ሰጠ፡፡ ጥቁሮች ከነጮች ጋር ያለአድልዎና ልዩነት ሳይደረግባቸው እኩል የትምህርት እድል የማግኘትና የመማር መብት አላቸው የሚል መደምደሚያ ላይ ተደረሰ፡፡ በዚሁ ውሳኔ የተበሳጨው "ጆርጅያ ኩሪዬር" የተባለ ጋዜጣ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በመቃወም ዳኞችን እንዲህ ሲል ገለፃቸው፡፡

  10147 Hits

ያልተመለሰ የገንዘብ ብድር ያለስምምነትና ያለማስታወቂያ/ያለማስጠንቀቂያ ወለድ ይቆጥራል?

የጉዳዩ መነሻ

ለዚህ አጭር ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 74950 የሰጠዉ ዉሳኔ ነዉ፡፡ ጉዳዩ የገንዘብ ብድርን ይመለከታል፡፡ ተበዳሪ ከአበዳሪ በታሕሳስ 26 ቀን 1995 የተወሰደዉን ብር 237000.00 በጥር 30 ቀን 1995 ለመመለስ ቃል ገብቷል፡፡ ነገር ግን ገንዘቡን ሳይመልስ በመቅረቱ የአበዳሪ ወራሾች በተበዳሪ ላይ ሐምሌ 21 ቀን 2002 ባስገቡት ክስ ተበዳሪ ዋናዉን ገንዘብ እንዲመልስና ከየካቲት 01 ቀን 1995 መሰረት የሚታሰብ ወለድም እንዲከፍል ዳኝነት ይጠይቃሉ፡፡ ተበዳሪ በበኩሉ በዉላቸዉ ዉስጥ ወለድ ይከፍላል የሚል ቃል እንደሌለና ማስታወቂያ/ማስጠንቀቂያ ስላልተሰጠዉ ወለዱን መክፈል እንደማይገደድ ይከራከራል፡፡ በዚህ ሙግት የተነሳዉና ይህ ጽሁፍ የሚዳስሰዉ ጥያቄም ይኸዉ ነዉ፤ ያልተመለሰ የገንዘብ ብድር ያለስምምነትና ያለማስታወቂያ/ያለማስጠንቀቂያ ወለድ ይቆጥራል?

  16428 Hits

Cassation No. 2239/2003 and Party Autonomy in Ethiopian Arbitration Law

Parties’ freedom to agree on any matter extends to agree to resolve their dispute either judicial litigation or arbitration. Arbitration is a system of dispute settlement where by disputants takes their case before arbitrators of their own choice. The civil code defines it “as a contract whereby the parties to a dispute entrust its solution to a third party, the arbitrator, who undertakes to settle the dispute in accordance with the principles of law.” (Art 3325(1)).

  14705 Hits

የውል ሕግ ይርጋዎች ከተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

በዚህ ጽሁፍ በፍትሐብሔር ሕጉ ስለ ውል በተደነገገው ክፍል ስር የተጠቀሱ አጠቃላይ የይርጋ ድንጋጌዎችንና በልዩ የውል ሕግ ክፍል በተለይም የስጦታ ውል፣ የአደራ ውል፣ የሽያጭ ውል ውልን መሰረት በማድረግ የተደነገጉ የይርጋ ድንጋጌዎችንና የመያዣ ውል ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ከሆኑ የሰበር ውሳኔዎች አግባብ ዳሰሳ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡

  4213 Hits