ስለ “የታሰሩ ሰዎች መብቶች” አንዳንድ ነጥቦች

 

በማያ ጋዜጣ ሐምሌ የታተመ በሰሞኑ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የችሎት ውሎዎች በፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የጋራ የወንጀል ሕጉን የማስፈጸም ተግባር ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የተለያዩ መንግስታዊ መሥሪያ ቤቶች ዳይሬክተሮችን ጨምሮ በሙስና ወንጀል ተጠርጣሪነት ተይዘው የጊዜ ቀጠሮ እየተጠየቀባቸው የሚገኙት እስከ ሣምንቱ አጋማሽ ድረስ ቁራቸው 45 የደረሱ ተጠርጣሪዎች በእሥር ላይ የሚገኙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የሕግ እርምጃው ቀጣይነት ያለው መሆኑንም በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በኢቢሲ መግለጫ ተነግሯል፡፡ የተጠርጣሪዎችን በእሥር ላይ መዋል ተከትሎ በመንግስትም ሆነ በግል መገናኛ ብዙሃን ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመውታል ተብሎ ስለተጠረጠሩበት ወንጀል ዝርዝር የገንዘቡን መጠን ጨምሮ በስፋት ሲዘገብ እየተመለከትንና በጋዜጦች እያነበብን ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎቹን በሕግ መሠረት በቁጥጥር ሥር አውሎ፣ ክስ አቅርቦ ጥፋተኝነታቸው በማስረጃ የተረጋገጠባቸውን በህጉ መሠረት እንዲቀጡ ማድረግ መሰረታዊ የህግ ዓላማ እንዲሁም አንደኛው የሕግ አስፈጻሚዎች ሥልጣንና ተግባር ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በእሥር ላይ የሚገኙት ተጠርጣሪ እሥረኞችን ሕገመንግሥታዊ መብቶችን የማክበሩ ጉዳይም ከተጠያቂነቱና የወንጀል ህጉን ከማስፈጸሙ እኩል ጎን ለጎን ትኩረትን የሚሻ ነው፡፡ የሰዎች መብቶችና ግዴታዎች ሁል ጊዜ ጎን ለጎን በትይዩ የሚፈጸሙ መሆናቸው መሠረታዊ የህግ መርህ ነው፡፡ 


ከላይ የተጠቀሱትን ተጠርጣሪዎችን ጨምሮ ካሁን በፊት በሙስናም ሆነ በሌሎች ወንጀሎች ተጠርጥረው በእሥር ቤት/ በማረሚያ ቤት በሚገኙ ተከሳሾች የፍርድ ቤት ችሎት ውሎዎች የታሰሩ ሰዎችን መብቶች በተመለከተ የሚነሱ ዘርፈ ብዙ የመብት ጥያቄዎች፣ የመብት ጥሰት አቤቱታዎችና ክርክሮች ተደጋግመው ሲነሱ ይስተዋላል፡፡ የዛሬው የጽሁፋችን ርእስና ጭብጥ ሆኖ የተመረጠው ይህንኑ የእስረኞችን መብት ጉዳይ የሚመለከት ነው፡፡ በኢፌዲሪ ሕገመንግስት ከአንቀጽ 13 እስከ 44 ስለ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ከተደነገጉት መካከል በአንቀጽ 21 ሥር በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች መብት ከሰብአዊ መብቶች መካከል አንደኛው ሕገመንግስታዊ መብት መሆኑን ተደንግጓል፡፡ 
የሕገመንግስቱ አንቀጽ 21 ሁለት ንዑሳን ድንጋጌዎች እንደሚከተለው ይነበባሉ፡- 
(1) በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች ሰብዓዊ ክብራቸውን በሚጠብቁ ሁኔታዎች የመያዝ መብት አላቸው፡፡

(2) ከትዳር ጓደኞቻቸው፣ ከቅርብ ዘመዶቻቸው፣ ከጓደኞቻቸው፣ ከሃይማኖት አማካሪዎቻቸው፣ ከሐኪሞቻቸው እና ከሕግ አማካሪዎቻቸው ጋር ለመገናኘትና እንዲጎበኟቸውም ዕድል የማግኘት መብት አላቸው፡፡

ለመሆኑ የታሰሩ ሰዎች ምን መብት አላቸው? መብቶቻቸውስ በየትኞቹ የሀገራችን ህግጋት ጥበቃ ተደርጎላቸዋል? የመብት ጥበቃውስ ከማን ነው? ጠባቂውስ ማን ነው? የት፣ መቼና እንዴትስ ይጠበቃል? ጽሁፉ እንዚህንና ተያያዥ ጭብጦችን ይዳስሳል፡፡

Continue reading
  13125 Hits

ያለ ፈጣን የፍርድ ሂደት ዋስትና የሚያስከለክል የወንጀል ድንጋጌ የሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 20 የሚፃረር ተግባር ስለመሆኑ

 

ዋስትና በሕገ መንግሥትም ሆነ የሕገ መንግሥቱ የበታች በሆኑ በርካታ ሕጎች የታፈረና የተከበረ መሠረታዊው ከሆነው የሰው ልጅ የመዘዋወር ነፃነትና ንፁሕ ሆኖ የመገመት መብት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ሰብዓዊ መብት ነው፡፡

የሰው ልጅ እንደፈለገ ለመዘዋወር ሁለት እግሮች የተሰጡት፤ በአንድ ቦታ ተወስኖ እንዳይቀመጥ ሰዋዊ ተፈጥሮ ነፃ አድርጎ የፈጠረው ይህን ተፈጥሮውንም አብዝቶ የሚወድ ነፃ ፍጡር ነው፡፡ ይህ ፍጡር አሳማኝ የሆነ ማስረጃ በማቅረብ አንዳች ወንጀል መፈፀሙ ካልተረጋገጠበት በስተቀር ንፁህ ሆኖ የመቆጠር መብትም አለው፡፡ 

ይህ ከላይ ከፍ ሲል የተገለፀው ነፃ ሰው በሕግ ከመዘዋወር ሊከለከል፤ በአንድ በተለየ ስፍራ ታስሮ ሊቀመጥ የሚችለው ለጠቅላላው ሕዝብ ጥቅም ሲባል፣ የጠቅላላውን ሕዝብ ጥቅም ከአደጋ ለመጠበቅ ከፍተኛ የሆነ ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝ ምንአልባት የተጠርጣሪውን የዋስትና መብት ማክበር ይህን የጠቅላላውን ህዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ ይህንን የጠቅላላውን የሕዝብ ጥቅም ለመታደግ ሲባል ብቻ አስቀድሞ በተቀመጠ ሕግ ሊገደብ የሚችል መሠረታዊ መብት ነው፡፡

የዚህ ጽሑፍ መነሻ ከመነሻው የዋስትና መብትን መገደብ ሕገ መንግሥታዊ ነው ወይስ አይደለም የሚል ሳይሆን ክርክርን በአጭር ጊዜ ለመጨረስ የሚያስችል ሥርዓት (speedy trial) መኖሩን እርግጠኛ ባልተሆነበት ሁኔታ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አንድ ወንጀል ፈፅሟል በሚል ክስ ስለቀረበበት ወይም ሊቀርብበት ስለሚችል ብቻ ዋስትና መከልከል ሕገ መንግሥታዊ ነው ወይ? የሚለው ነው፡፡

Continue reading
  11138 Hits
Tags:

(Non) retroactivity of Ethiopian Criminal Law


1. Introduction

A criminal law may be changed owing to various reasons. Obsoleteness, loopholes and insufficiency of penalties on the part of the existing criminal law are some of the justifications which may warrant its amendment or replacement. Even though changing a criminal law following changes in circumstances is vital and advisable, the advent of a new criminal law may create the difficulty of determining the temporal scope of application of the former and the new laws. An interesting solution for such problem is the principle of nonretroactivity of criminal law, which states that a criminal law is applicable only to offences committed subsequent to its enactment. Nevertheless, this principle has some exceptions, which allow the retrospective application of a criminal law.

The purpose of this article is, therefore, to explicate the meanings of and justifications for the (non) retroactivity of criminal law, to show how they are incorporated and how they must be comprehended under Ethiopian criminal law.

2.  (Non)retroactivity of Criminal Law

The word “retroactive” denotes “extending in scope or effect to matters that have occurred in the past”. It follows that retroactive legislation, also known as ex post facto laws, are “[l]aws which, expressly or by implication, operate so as to affect acts done prior to their having been passed.” In the context of criminal law, retroactivity is “to make an action a crime that was not a crime at the time it was done.” As such, retroactivity of criminal law “means that even a person well-informed about the law will be ignorant of the illegality of her or his acts because those acts are not deemed illegal until the retroactive law is made.” Conversely, the notion of nonretroactivity of criminal law suggests that criminal law should be applicable only to crimes done after the coming into force of the law.

Continue reading
  16216 Hits

በወንጀል ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔን እንደገና ስለማየትና በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ

 

መግቢያ

በወንጀል ጉዳይ  የፍርድ ውሳኔ የሰጠው ፍርድ ቤት በድጋሜ ጉዳዩን ማየት ማለት ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ከሰጠ በኋላ የግዜ ገደብ ሳይኖረው ጉዳዩን በድጋሜ በተለያዩ ምክንያቶች ማየትና በድጋሜ ውሳኔ መስጠት ማለት ነው፡፡ በተለይም በዚህ ዘመን የሐሰት ሰነዶች የመቅረባቸው ጉዳይ እራስ ምታት በሆነበት፣ ሐሰተኛ ምስክርነትን መሠረት በማድረግ በተቃራኒ ተከራካሪ ወገንም ሆነ በፍርድ ቤቱ ሊደረስበት ባለመቻሉ የተሳሳተና የተዛባ የፍርድ ውሳኔ በሚሰጥበት ዘመን የእነዚህን ሐሰተኛ ማስረጃዎች ግዜ ሳይገድበው የሚያገኝ የወንጀል ጉዳይ ተከራካሪ ወደዛው ፍርድ ቤት በመሄድ የተገኘውን አዲስ ማስረጃ መሠረት በማድረግ ክርክር በድጋሜ አድርጎ ውሳኔው እንዲሰተካከል ለማድረግ የሚያስችል የሕግ አካሔድ መኖሩን አስፈላጊነት ሁሉም የሚስማማበት ነው፡፡ አንዳዴም እንደሚሰማው በህይወት ያለን ግለሰብ ገድለኃል ተብሎ ጥፋተኛ የተባለን ግለሰብ ሞተ የተባለው ግለሰብ በህይወት መኖሩ ቢታወቅ እንኳን ጥፋተኛ የተባለውን ግለሰብ ነፃ የሚያወጣ የሕግ አካሔድ ሊኖር የሚገባ ስለመሆኑም የሚያስማማ ነው፡፡ በቅርብ ግዜ በተላለፈ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ከሚያጋጥማቸው ጉዳዮች በመነሳት የሐሰት ሰነዶች እና የሐሰት ምስክርነት ጉዳይ ከግዜ ወደ ግዜ እየተበራከተ መምጣቱን ሲናገሩ መስማቴ ትዝ ይለኛል፡፡ ይህን መሰል የፍትሕ ጠር የሆነ ተግባር ሙሉ ለሙሉ ማጥፋት ባይቻል እንኳን ይህ ሁኔታ በታወቀ ግዜ ግን ጉዳዩን ውሳኔውን የሰጠው ፍርድ ቤት በድጋሜ እንዲያይ የሚያስችልና ሐሰተኛውን ማስረጃ እና የተሳሳተውን ውሳኔ ለማስተካከል የሕግ መሠረት ሊኖረን ይገባል፡፡

የሕጎች አጭር ቅኝት

አሁን በሥራ ላይ ያለው የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት በወንጀል ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በይግባኝ በተቀመጠው 15 ቀን ውስጥ የውሳኔውን ግልባጭ መጠየቂያ እንዲሁም የውሳኔ ግልባጩ ከደረሰ 30 ቀን ውስጥ የይግባኝ አቤቱታውን ውሳኔውን ከሰጠው ፍርድ ቤት አንድ ደረጃ ከፍ ብሎ ላለ ፍርድ ቤት በተሰጠው ወሳኔ ላይ ውሰኔውን በሰጠው ፍርድ ቤት መዝገብ ቤት በኩል ይግባኝ ከማለት በስተቀር (የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ ቁጥር 182187/1/ እና /2/ መመልከት ይቻላል) አዲስ የሆነና ሐሰተኛ ማስረጃ ስለመቅረቡ የሚያስረዳ ማስረጃ አግኝቻለሁ በማለት ፍርዱን ለሰጠው ፍርድ ቤት ውሳኔውን በድጋሜ ለማየት አቤቱታ ለማቅረብ የሚያስችል የሕግ ድንጋጌ የለም፡፡ በይግባኝ ቢታይም እንኳን አዲስ ማስረጃ ሊሰማ የሚችለው የይግባኝ ፍርድ ቤቱ የመሰማቱን ጉዳይ ካመነበት ብቻ ነው ይህም ሁኔታ በጠባቡ የሚታይ ነው(የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ ቁጥር 194/1/ መመልከት ይቻላል)፡፡ ከወንጀል ጉዳይ በተቃራኒው በፍትሐብሔር ጉዳይ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ ቁጥር 6(1)() እና () የመጨረሻ ፍርድ ወይም ውሳኔ ወይም ትዕዛዝ የተሰጠው በሐሰት ተዘጋጅቶ የቀረበውን ሰነድ ወይም ሐሰተኛ ምስክርነት ቃልን ወይም መደለያን ወይም ወንጀል ጠቀስ የሆነ ተግባርን መሠረት በማድረግ ሲሆንና አቤት ባዩም ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት አስፈላጊውን ትጋት አድርጎ ለማወቅ ያለመቻሉን ለማስረዳት የቻለ እንደሆነ እና እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ተግባሮች መፈፀማቸው ቢገለፅ ኖሮ ለፍርዱ መለወጥ ወይም መሻሻል በቂ ምክንያት ሊሆኑ ይችሉ እንደነበረ ለማስረዳት የቻለ እንደሆነ በእነዚህ ምክንያቶች መነሻነት ፍርዱን ለፈረደው ወይም ትዕዛዝ ወይም ውሳኔውን ለሠጠው ፍርድ ቤት የተወሰነውን የዳኝነት ክፍያ በመክፈል አቤቱታውን ለማቅረብ እንደሚችል በግልፅ ያስቀምጣሉ፡፡

Continue reading
  11151 Hits

ችሎት መድፈር፡- ሕጉ እና የአሠራር ግድፈቶች

 

 

የኢፌድሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 449፦

449. ፍርድ ቤትን መድፈር

(1) ማንም ሰው በፍርድ ቤት ምርመራ በሚደረግበት ወይም የፍርድ ሥራ በሚከናወንበት ጊዜ፦

Continue reading
  12632 Hits

ስለቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) ፍርድ ቤት ተልዕኮ፣ ሥልጣን እና ተግባር

 

መግቢያ

በዘመናዊ አሠራር የወንጀል ጉዳይን እንዲከታተል የተቋቋመ እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለፍርድ ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዩች አይነትና ብዛት ለመለየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ይቀይስለታል፡፡ ይህ እንዲሆን የሚያሰፈለገውም በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በሚከሰሰበትና ለፍርድ በሚቀርብበት ጊዜ ብዙ ችግር ሊገጥመው እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ በወንጀል ተግባር ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ ሰው የሚደርስበት የማሕበራዊና የኢኮኖሚያዊ ቀውስ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ አይነቱ ከባድ ጉዳት ሊደርስ የሚገባው በእርግጥ ወንጀል በሰሩና ወንጀል ለመስራታቸውም የማያጠራጠር ማስረጃ በቀረበባቸው ሰዎች ላይ መሆን አለበት፡፡ አንድን ሰው ወንጀል ሰርተሃል ብሎ መክሰስና በማሕበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለውን ክብር ዝቅ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ክሱን በማስረጃ ማረጋገጥና ተከሣሹን ጥፋተኛ ማስደረግ ግን በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ በማስረጃ ሊረጋገጡ የማይችሉ ወንጀሎች በተቻለ መጠን በአጭሩ መቋጫ እንዲያገኙ ማድረግ የመንግሥት ሃላፊነት ነው፡፡

ሁለተኛ የወንጀልን ጉዳይ በፍጥነት ውሣኔ ማሰጠት ሲገባ በልማድ እንደሚታየው ግን ይህን ማድረግ እንዲህ ቀላል ሆኖ አልተገኘም፡፡ በማንኛውም አገር እንደሚታየው የወንጀል ሥራ በየአቅጣጫው እየጨመረ በመሄድ ላይ የሚገኝ ቢሆንም እንኳን ሁሉንም ወንጀል አድራጌዎች ወዲያውኑ ወደ ፍርድ ቤት ለማቅረብና ለማስቀጣት አይቻልም፡፡ ከወንጀሎቹ ብዛት አንፃር ሲታይ ደካማወቹ ጉዳዩች በአጭሩ የሚቋጩበት ዘዴ መኖር አለበት፡፡ ከማስረጃ አኳያ ጠንካራዎቹን እና ደካማዎቹን ጉዳዩች የምናጣራበት ዘዴ ቀዳሚ ምርመራ በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ጠንካራዎቹን እና ደካማዎቹን ጉዳዩች የማበጠሩና የመለየቱ ተግባር እንደየ አገሩ የሕግ ሥርዓት ለዐቃቤ ሕግ ወይም ለመርማሪ ዳኛ (investigating Judge) ወይም የሕግ ሙያ ለሌላቸው እማኝ ዳኞች (Grand juries) ሊሰጥ ይችላል፡፡ ከፖሊስ የምርመራ መዝገብ የደረሰው ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩ በቀዳሚ ምርመራ አድረጌ ፍርድ ቤት መጣራት የሚገባው ሆኖ ካገኘው ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን እንዲያጣራ ሊያዝ ይችላል፡፡ ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩ ለቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ የሚሰጠው ምን ምን ሁኔታዎች ተሟልተው ሲገኙ ነው? ጉዳዩ ለቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት ሣያቀርብ በቀጥታ ክሱን በዳኝነት ለማየት ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ቢያቀርብ ሊመጣ የሚችለው ውጤት ምንድን ነውየቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት ሥልጣን ተግባርና ዓላማ ምንድን ነው?

ከላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሽ ለማገኘት ቀዳሚ ምርመራን (ቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) በሌሎች ሐገራት Preliminary Hearing, Preliminary Examination ወይም Examining Trial በመባል ይጠራል) አስመልክቶ በሌሎች ሐገራት ያለውን የሕግ ማዕቀፍ ይዘትና አሠራር በቅድሚያ መመልከት አስፈላጊ ነው፡፡

Continue reading
  13435 Hits

የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145 አፈፃፀም ላይ የሚስተዋል መሠረታዊ የአሠራር ግድፈት

በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145 ላይ አንድ ምስክር በፖሊስ ምርመራ ወቅት የሰጠው ቃል ዓቃቤ ሕግ ወይም ተከሳሹ ባመለከተ ጊዜ የተሰጠውን ምስክርነት ርድ ቤቱ ሊመለከተው እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ ይህ መብት የተሰጠው ለዓቃቤ ሕግ እና ለተከሳሽ በእኩል ደረጃ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ በሚባል አኳኋን እየተጠቀመበት ያለው ዓቃቤ ሕግ ነው፡፡ ዓቃቤ ሕግ በማስረጃነት የቆጠረው ምስክር በማንኛውም ምክንያት በችሎት ቀርቦ መመስከር ባልቻለ ጊዜ ሁሉ ዓቃቤ ሕግ የሚጠቅሰው ሥነ ሥርዓት የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145 ነው፡፡ በችሎት የቀረቡ ምስክሮች አጠራጣሪ ወይም የቀረበውን ክስ በሚገባ የማያስረዱ ሲሆን ዓቃቤ ሕግ ፊቱን ወደ 145 ያዞራል፡፡ 145 የዓቃቤ ሕግ የማስረጃ ክፍተት ማሟያ እየሆነ መጥቷል፡፡ ፍርድ ቤቶችም ይህንንኑ ለፖሊስ የተሰጠ የምስክርነት ቃል በአብዛኛው ተቀብለው በማስረጃት ሲጠቀሙበት ይሰተዋላል፡፡

የዚህ ጽሑፍ መሠረታዊ ማጠንጠኛም የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145 ያለአግባብ በዓቃቤ ሕግና በፍርድ ቤቶች ጥቅም ላይ ውሏል የሚለው ነጥብ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ይህን ሁኔታ በሚከተሉት ሦስት ነጥቦች እንዴት ተገቢ እንዳልሆነ ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡

1.  በተከሳሹ መስቀለኛ ጥያቄ፣ በፍርድ ቤቱማጣሪያ ጥያቄ ያልቀረበለት፣ ተገቢው መኃላ ፈጽሞ ምስክርነቱን ያልተሰጠንምስክርነት ቃል በማስረጃነት መቀበል ሕገ መንግሥታዊ ስላለመሆኑ

አንድ ተከሳሽ ጥፋተኛ እስኪባል ንፁህ ነው፡፡ ይህ ንጹህነቱ ጥፋተኛ እስኪባል ድረስ ከሚረጋገጥባቸው የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ደረጃዎች አንዱ የቀረበበትን ምስክር በጥያቄዎቹ መፈተን ሲችል ነው፡፡ ተከሳሽ የቀረበበትን ምስክር ሲጠይቅ ለፍርድ ቤቱ የሚያሳየው እውነት ከመኖሩም ባላይ ፍርድ ቤቱ ስለ ምስክሩ ታማኝነት፣ ስለምስክርነቱ ክብደት እና ተገቢነት የሚረዳው እውነት ይኖራል፡፡ በተከሳሽ መስቀልያ ጥያቄ ያልቀረበለት ምስክር ምስክር ሳይሆን ቃል አቀባይ ነው፡፡ በጥያቄ የሚመሰከረው ምስክርነት እውነትና ያልተመረመረ ምስክርነት ምስክርነት ሳይሆን የአቋም መግለጫ ነው፡፡ ለዚህም ነው በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20 ላይ የተከሰሱ ሰዎች የቀረቡላቸውን ምስክሮች የመጠየቅ መብት የተጎናጸፉት፡፡ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 136 እና ተከታዮች ድንጋጌዎችም ስለምስክርነት ሥርዓት ቁልጭ ተደርጎ ተቀምጧል፡፡ በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንድ ምስክር በአንድ ተከሳሽ ላይ እንዲመሰክር ሲደረግ ስለ እውነት በሚያምንበት ነገር የመማል በሚመሰክርበት ጊዜ ለተከሳሽ መስቀልያ ጥያቄዎች እንዲሁም ለፍርድ ቤቱ የማጣሪያ ጥያቄዎች ተገቢውን መልስ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡ ምናልባትም እንደ ክርክሩ ደረጃ ከኤግዚቢቶች፣ ቀደም ሲል ከተሰጠው ምስክርነት ከነገሮች ጋር የተዛመዱ ፈታኝ የመስቀልያ ጥያቄዎች ይቀርቡለታል፡፡ በነዚህ ሂደቶች አልፎ የሰጠው ምስክርነት ከጉዳዩ ጋር ተገቢነት ያለው፣ የማስረዳት ክብደቱ ከፍተኛ የሆነ፣ እምነት የሚጣልበት ምስክርነት ሰጥቶ ከሆነ በርግጥም ተከሳሹ በዚህ ምስክር ምስክርነት ንጹህ ሆኖ የመገመት ካባው ወልቆ ጥርጣሬ ላይ ሊወድቅ ይችላል፡፡ ይህን ማስተባበል ባለመቻሉም ወንጀለኛ ተብሎ ቢፈረጅ የፍትሕ ሥርዓቱ የሚፈልገው ተገቢ ሁነት ነው እና እሰይ እንጂ ለምን ሊባል አይችልም፡፡

በሕገ መንግሥቱም ሆነ በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተቀመጡ የመማል፣ በክስ ሂደቱ የቀድሞ ጥፈተኝነት ያለመግለፅ፣ ዋና ጥያቄ መስቀለኛ ጥያቄ እና ድጋሜ ጥያቄ የመጠየቅና የመጠየቅ፣ በተለየ ሁኔታ ካልሆነ በስተቀር በግልፅ ችሎት የመዳኘት፣ ጉዳዮች ዓላማው በተድበሰበሰ፣ ግልፅነት በጎደለው፣ ተገቢው ጥያቄ ባልቀረበበት፣ እምነት በማይጣልበት፣ ሀሰት በሆነ ምስክርነት ንፁህ የሆኑ ሰዎች ወንጀለኛ እንዳይባሉ ለመከላከል ለተከሳሹ መብት ዘብ ያቆማቸው መሠረታዊ የወንጀል ክርክር መግለጫዎች ናቸው፡፡ በእነዚህ ሂደቶች ያላላፈን በአንድ ወቅት ፖሊስ ሲጠይቀው ለፖሊስ የሰጠው ቃል ለጠፋ ምስክር፣ ለተንሻፈፈ ማስረጃ፣ ለጎደለ ምስክርነት ማሟያ የምናደርገው ከሆነ ከፍ ሲል የተገለፀው መሠረታዊ የወንጀል ክርክር ሂደቶችን አስፈላጊነት መካድ ይሆንብናል፡፡

Continue reading
  17894 Hits

"በሕግ አግባብ"ያለአግባብ ስለመታሰር

 

ካሳ አልባ የፍትሕ ሥርዓቱ ተጎጂዎች

እንዲያው አያድርገውና በወንጀል ተጠርጥረው ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብዎ አስቸጋሪውን የወንጀል ምርመራ ተቋቁመው ካለፉ በኋላ በዓቃቤ ሕግ ተከሰው የዋስትና መብትዎን ተከልክለው ክራሞትዎ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሆነ እንበል፤ በሕግ ጥላ ሥር፡፡

የፍርድ ቤት ቀጠሮዎት በደረሰ ጊዜ እጅዎ በካቴና ተጠፍንጎ ወይም ከሌላ እስረኛ ጋር ተቆራኝቶ ጠመንጃ በወደሩ ፖሊሶች በአይነ ቁራኛ እየተጠበቁ ለወራት ወይም ለዓመታት ነጻነትዎ ተነፍጎ የፍርድ ሂደቱን ሲከታተሉና ሲሟገቱ ከባጁ በኋላ በመጨረሻ ጉዳይዎትን ይመለከት የነበረው ዳኛ የችሎቱን ጠረጴዛ በመዶሻው ግው! በማድረግ ‹‹ከተከሰሱበት ወንጀል በነፃ ተሰናብተዋል ቅንጣት ያህል ጥፋት የለብዎትም›› ብሎ ቢያሰናብትዎ ምን ይሰማዎታል???

እርግጥ ነው፣ ተሟግተው በማሸነፍዎና ንጹህነትዎን በማስመስከርዎ አልያም የእሥር ህይዎትዎ በማክተሙና ፀሐይቱን ያለ አንዳች ከልካይና ተቆጣጣሪ እንዳሻዎ ሊሞቋት በመብቃትዎ ደስታ እና እፎይታ እንደሚሰማዎ አያጠራጠርም፡፡

Continue reading
  12305 Hits

በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት የቀዳሚ ምርመራ ድንጋጌዎችና አተገባበራቸው አጭር ዳሰሳ

 

መግቢያ

የወንጀል ክስን በማስረጃ አስደግፎ በማረጋገጥ እና ተከሳሽን ወደ ፍርድ ቤት በማቅረብ ጥፋተኛ ማስደረግ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ትልቅ ጥረትና ድካም የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡ አንድ ወንጀል ማህበረሰቡ ላይ ሲፈጸም ወንጀሉን የፈጸመን አካል ነቅሶ በማውጣት ለፍርድ በማቅረብ ማስቀጣት የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ አንድ መንግሥት የሕዝብን  ሥልጣን  ሲቀበል  የማህበረሰቡን  ሰላም  መጠበቅ ከሕዝቡ የተጣለበት  ግደታው  ነው፡፡ ይህንን ሰላም ለመጠበቅ  ደግሞ  ወንጀል  እንዳይፈፀም ይከላከላል፡፡ ከተፈፀመ በኋላ ፈፃሚውን ለሕግ ያቀርባልወንጀል ለመፈፀሙ ሊያሥረዱ የሚችሉ ማስረጃወችን አብሮ ያቀርባል፡፡

ቀዳሚ ምርመራም መንግሥት ወንጀል መፈፀሙን ለማሥረዳት የሚችሉ ማስረጃወችን የሚሰበስብበት አንዱ መንገድ ነው፡፡ ቀዳሚ ምርመራ ክስ ከመሰማቱ በፊት በፍርድ ቤት የሚደረግ የማስረጃ መስማት እና ለክስ መስማት የሚቀርበውን ጉዳይ የመለየት ሂደት ነው፡፡

የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት በሦስተኛ መጽሐፉ ከአንቀፅ 80 እስከ 93 ድረስ ስለ ቀዳሚ ምርመራ የሚያትቱ ድንጋጌዎች አካትቶ ይገኛል፡፡ ይህ ጽሑፍ የሚያተኩረው በሃገራችን ያለውን የሕግ ማዕቀፍ ይዘት እና የተግባር አሠራር የሚመለከት ነው፡፡ በአተገባበር ደረጃ ግድፈት አለባቸው ተብለው በጸሐፊው እይታ የታዩ ደንጋጌዎች ላይ ያተኮረ ነው፡፡ እስከተቻለ ድረስ የሕጉን መንፈስ እና በተግባር ምን እየተሠራ እንደሆነ ለማሳየት ተሞክሯል፡፡

Continue reading
  23372 Hits

What is Organized Crime?

1.  Introduction

Distinct from conventional crimes, “organized crime” involves the commission of series crimes by criminal groups. The offences range from the traditional piracy and slave trade to the present day cybercrime and nuclear smuggling. The Italian Mafia, the Chinese Triads, the Colombian drug cartels, the Japan Yakuza and the Nigerian Criminal Groupsare examples of organized criminal groups.

Organized criminal groups are booming dramatically throughout the world. Just looking at the known Mafias, there was an increase from 785 in 1990 to 8 000 in 1996. Besides, the escalation in figure, the problem gets worse, as organized crime causes massive damage compared to ordinary crimes. For instance the damage cause by organized crime in a year is estimated 13 to 19 billion $ USD for Australia, while, it reached 42.2 billion$ USD for Canada. 

Noticing the problem, international as well as national initiatives are projected to combat organized crime. On top of other things, the fight against organized crime necessitates clear definition. This is crucial, as practitioners as well as academicians need to have a clear understanding of the concept in order to analyse and tackle the problem effectively.

This paper will discuss the concept of “organized crime” as defined under international and national laws. Moreover it will look at the structure, operation, aims and victims of organized crime. It also critically analyses the present definition of “organized crime”. Last but not least, based on the discussion and critics, it will suggest solutions on how to define “organized crime”.

Continue reading
  9444 Hits