የኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ከአዲስ አበባ ምን ሊሆን ይችላል

 

በሀገራችን በቅርብ ጊዜየቶች ውስጥ በተደጋጋሚ እየተነሱ ከሚገኙ ጉዳዮች እና የሕግ እና የፓለቲካ ተዋንያንን እያነጋገር ያለው አንዱ ጉዳይ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከአዲስ አበባ ከተማ ሊኖረው ይገባል በሚል በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 49 (5) የተቀመጠውን ልዩ ጥቅም የተመለከተው ድንጋጌ ነው፡፡በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ አንዳንድ ሰዎች እንደሚያነሱት በሀገሪቷ ውስጥ ያሉትን ሰለማዊ የሆኑ ህዝቦች አብረው ሲኖሩ የነበሩትን ግንኙነት ለማበላሸት እና ልዩነትን ለማጉላት በሚል የተቀመጠ ድንጋጌ አድርገው የሚመለከቱ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ይህ ድንጋጌ በሀገሪቷ ውስጥ የነበረውን ተጨባጭ የህዝቦች ችግር ለመፍታት በሚል የገባ ችግር ፈቺ እና ምክንያቲያው ድንጋጌ እንደሆነ አድርገው ይገልጹታል፡፡ በዚህ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ላይ ሕገ-መንግሥቱ ለሕገ-መንግሥት አርቃቂ ጉባኤ ቀርቦ በሚታይበት ወቅትም ቢሆን የተለያዩ ሀሳቦች የተነሰቡት እና በሃላም ላይ ድንጋጌው ተቀባይነት አግኝቶ የጸደቀበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተደነገገው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ አለው የሚለው ድንጋጌ ይዘት ላይ ምን እንደሆነ እና ምን እንዳልሆነ፤ እነዚህን ልዩ ጥቅሞች በስራ ላይ ለማዋል በሚታሰብበት ውቅት ታሳቢ ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጉዳዮች በመግለጽ ለውይይት የሚሆን መነሻ ሀሳብ ማቅረብ ነው፡፡

የኦሮሞ ህዝብ የብዙ ሺህ ዘመናት አኩሪ ታሪክ ያለው፤ ዘመናው የዲሞክራሲ እሴቶች የሆኑ የመንግሥት አመራር እና አስተዳደር የነበራቸው፤ የራሱ የዘመናት አቆጣጠር፤ አኩሪ ባህላዊ እሴቶች ያሉት ህዝብ ነው፡፡ይህ ህዝብ እንደማናኛውም ህዝብ የነበረው ስልጣኔ እየወደቀ እየተነሳ፤ ከሌሎች ጎረቤት ህዝቦች ጋር ሰላማዊ የሆነ ተቻችሎ የመኖር ባህሪያቶችን ይዞ የኖረ እና እየኖረ የሚገኝ ህዝብ ነው ቢሆንም የራሱን ባህል፤ ቋንቋ ታሪክ እና ሌሎች የማንነት መገለጫዎች እንደ ሃላ ቀር በመቅጠር በፊት የነበሩት የንጉሳዊያን አስተዳደሮች በህዝቡ ላይ እጅግ አሳዛኝ እና ታሪክ ሊረሳው የማይችል ድርጊት ሲፈጽሙ ቆይተዋል፡፡ሕዝቡ ሲፈጸሙበት የነበሩትን ድርጊቶች አንዳንዴ በተደራጃ እና በአብዛኛው በተበታተነ መልኩ ሲታገል እና ሲቃወም ቆይቶ ራሱ በላካቸው ወኪሎቹ መሰረት በ1987 ዓ.ም የጸደቀውን የኢፌደሪ ሕገ-መንግሥት የክልል ባለቤት ሊሆን ችሎዋል፡፡ ህዝቡ የራሱ የሆነ ክልል እንዲኖረው ማድረጉ ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች እና የተለያዩ ክልላዊ አስተዳደሮች ጋር ሊኖረው ስለሚገባው ግንኙት ምን መምሰል እንዳበት በሕገ-መንግሥቱ ላይ ደንግጎዋል፡፡ በዚህ አግባብ በሕገ-መንግሥቱ ላይ ከተቀመጡት መሰረታዊ ጉዳዮች አንዱ ክልሉ ከአዲስ አበባ ከተማ ላይ ልዩ ጥቅም ሊኖረው የሚገባ እንደሆነ የሚያስቀምጠው ድንጋጌ አንዱ ነው፡፡በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተቀመጠው ፌደራላዊ ስርዓት መሰረታዊ እምነቱ ብዙሀነትን ማዕከል ያደረግ አንድነትን መፍጠር እንደሆነ በመግቢያው ላይ ደንግጎዋል፡፡

ሕገ-መንግሥቱ ላይ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ላይ አለው የሚለው ድንጋጌ ልዩ ጥቅም የሚባሉ ሊጠበቅላቸው/ሊንጸባረቅባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ምን እንደሆነ ያመለከተ እንጅ ልዩ ጥቅም ለሚለው ሀረግ የሰጠው ትርጉም የለም፡፡ ልዩ ጥቅም የሚለውን ሀረግ ሲታይ ልዩ የሚለው ቃል ከአንድ ነገር ጋር የተያያዘ እና ከተለመደው ወጣ ያለ የሚለውን ሁኔታ የሚገልጽ ሲሆን ጥቅም የሚለው ደግሞ ህጋዊ ተቀባይነት ያለው አንድ ጉዳይ ላይ ሊኖር የሚችለውን መብት የሚመለክት እንደሆነ ሊወሰድ ይችላል፡፡ስለሆነም ክልላዊ መንግሥቱ  በአዲስ አበባ ላይ ልዩ ጥቅም አለው ሲባል ተለይቶ የሚታወቅ ሕገ-መንግሥታዊ መብት የሚያጎናጽፍ ጥቅም አለው ተብሎ ይወሰዳል፡፡

ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 49 ላይ ለክልሉ መንግሥት ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ላይ እንዲጠበቅ የፈለገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ሕገ-መንግሥቱ ሲዘጋጅ በአንቀጹ ላይ ከተካሄዱ ወይይቶች፤ ከፌደራል ስርዓቱ መሰረታዊ ባህሪያት እና መነሻ ምክንያቶች አንጻር የሚከተሉት ሊሆኑ እንደሚችሉ ይወሰዳል፡፡

Continue reading
  12306 Hits

የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ጥያቄና ሕገ መንግሥቱ

 

መግቢያ

የማንነት ጥያቄ ምንድን ነው? የድንበር አከላለል ለውጥ (የድንበር ውዝግብ) ጥያቄስ ምንድን ነው? የኢትዮጵያ ሕግስ እንዴት ነው የሚጠብቃቸው? የዚህ ማስታወሻ ዓላማ እነዚህን ጉዳዩች ስለሚመለከቱት የሕግ ክፍሎች በማጥናትና ስለአተረጎማቸው አስተያየት በማቅረብ እነዚህን ጥያቄዎች መመለስ ነው፡፡ ከእነዚህ ባሻገር ይህ ማስታወሻ ስለ ትግራይ ሕዝብ መልክዓ ምድራዊ አሰፋፈር ታሪካዊ ዳሰሳ ባጭሩ አድርል፡፡

ይህን ማስታወሻ ለመጻፍ ያነሳሱኝ ነገሮች የፌዴሬሽን ምክር ቤት የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ ተወካዮች በቀረበለት በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀጽ 20 ድንጋጌ መሠረት የማንነት ጥያቄው በክልሉ በደረጃው ባሉ የአሰተዳደር እርከኖች ታይቶ ውሳኔ ማግኘት የሚገባው በመሆኑ ጉዳዩ በትግራይ ክልል እንዲታይ ብሎ በመወስን ማስተላለፉ እና የእኔ ማንነት ናቸው፡፡ በዚህ የተነሳ ዋናው ጥያቄ  የሆነውን የማንነት ጥያቄ ምንነትና የድንበር አከላለል ለውጥ (የድንበር ውዝግብ) ጥያቄ ምንነት በመመርመር ስለአተረጎገማቸው አስተያየት ማቅረብ ወደድኩኝ፡፡

1.    የማንነት ጥያቄ ባሕርይ ጥያቄውን የማቅረብ መብት    

Continue reading
  13754 Hits

የቴዲ አፍሮ አልበም ምርቃት ክልከላ እና የመሰብሰብ መብት

 

መንደርደሪያ

የዚህ ጽሑፍ መነሻ የቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ መከልከል ሲሆን ጽሑፉ ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት በማንኛውም ምክንያት መሰብሰብ አድማሱ እስከምን ነው? የሚለውን መሠረታዊ ነጥብ የሚዳስስ ሲሆን የአልበም ምርቃቱን መከልከል ምክንያቶች በተመለከተ ግን ጸሐፊው በሁለቱም ወገኖች በኩል ያለውን እውነት በማስረጃ ባለማረጋገጡ አቋም ከመያዝ ተቆጥቧል፡፡ ይሁን እንጂ አጋጣሚው በአስፈፃሚውም ይሁን በስብሰባ አዝጋጆቹ ብሎም በማህበረስቡ ላይ ያለውን መደናገር የመሰብሰብ መብትን አድማስ ለማብራራት ምቹ በመሆኑ ጸሐፊው በርግጥ ለቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ ፈቃድ ያስፈልግ ነበር? ፈቃድ ካስፈለገውስ መከልከል ይቻል ነበር? የመከልከል ተግባሩ የሚጥሳቸው መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችና መብቶችስ ምንምን ናቸው? ለሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ይሞክራል፡፡

መግቢያ

መሰብሰብ ሰው ሁለት ሆኖ ከተፈጠረበት የታሪክ አውድ ይጀምራል፡፡ ሰው ማህበራዊ እንስሳ ነው ሲባል በሌላ አነጋገር ሰው ይሰበሰባል እንደ ማለት ነው፡፡ ፈጣሪም አዳም ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ሲል ጥንትም ፈጣሪ ሰውን ሲፈጥረው በውስጡ ከሌሎች ጋር የመሆን፣ ከሌሎች ጋር የመምከር፣ ከሌሎች ጋር የመደሰት፣ የመኖር፣ አንድን ነገር በጋራ የማድረግ፣ የማክበር ባሕርይ እንደፈጠረበት ሲያጠይቅ ነው፡፡ እናም መሰብሰብ ከፍ ሲል ፈጣሪ ለአዳም/ለአደም ሄዋንን/ሃዋን ሲፈጥርለት ዝቅ ሲል አዳምና ሄይዋን ቃዬልን ጠርተው ስለ አቤል ጉዳይ ሲጠይቁት ይጀምራል፡፡

Continue reading
  11765 Hits

ጥቂት ስለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የኢትዮጵያ መስፈርት ከአለምፍ ሕግ ጋር ሲቃኝ

 

ሀገሮች የዜጎቻቸውን የንብረት፣ የህይወት በአጠቃላይ የስብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ የተለያየ ሕጎችን ያወጣሉ፡፡ እነዚህም ሕጎች ከሕገ-መንግስቱ (የየሃገሩ የበላይ ህግ) ጨምሮ አዋጆችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን ያካትታል፡፡ በእነዚህ ሕጎች የተደነገጉት መብቶችን ማራመድ አንዳንድ ጊዜ የሌላውን ሰው መብትና ደህንነት አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል፡፡ በእንደዚህ ሁኔታ ላይ ሲሆን ሕግ እነዚህ መብቶች ላይ ገደብ (limitation) ያስቀምጣል፡፡ ይህ የመብት ገደብ ዘለቄታና በቋሚነት የሚፀና ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል በሕገ- መንግስታችን አንቀፅ 29 ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ተደንግጓል ፡፡ ነገር ግን በተመሳሳይ አንቀፅ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ወጣት ዜጎችን እና የሌሎች ሰዎች መብትና ክብር ለመጠበቅ ሲባል በህግ ሊገደብ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ ይህ የመብት ገደብ ሲሆን ተፈፃሚነቱም በዘለቄታዊነት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመብት ገደብ ነገሮች ተፈጥሮዊና በተለመደው ሥርዓት ላይ እያሉ የሚተገበር ነው፡፡

በአንፃሩ አንድ ሀገር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ (state of emergence) የምታውጀው አንድን ክሰተት ባለው ነባርዊና በተለምዶ በተዘረጋው ሥርዓት መቆጣጣር ሳይቻል ሲቀር እንዲሁም የሀገሪቱን ህልውና የሚፈታተን አደጋ ሲያጋጥም ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲያጋጥም በሕግ የተደነገጉ መብቶችን ሁሉ ተግባራዊ ላድርግ ማለት አዳጋች አንዳንዴም የማይቻል ሊሆን ይችላል ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ሰፊው የስብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ሊገደቡ ይችላሉ፡፡ ይህ የመብት ገደብ ከላይ ከጠቀስነው የመብት ገደብ የሚለየው ነገር ቢኖር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወቅት የመብት ገደብ ዘላቄታዊ ሳይሆን ጊዜያዊ ነው፡፡

የተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስምምነቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመደንገግ እና በዚህም የተነሳ መብቶች ሊገደብ እንደሚችሉ እውቅና ይሰጣሉ፡፡ እነዚህም ዓለም አቀፍ ስምምነቶች  ይህንን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመደንገግ መብት ሲሰጡ በተመሳሳይ መልኩ ምን ምን የሥነ-ሥርዓት (procedural requirements) እና የይዘት (substantive requirements) መስፍርቶችን መሟላት እንዳለባቸው ደንግገዋል፡፡

  1. የይዘት መስፈርቶች

ሀ. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ  እጅግ አስፈላጊ መሆን አለበት (necessity test)

Continue reading
  9727 Hits

Making Extraordinary Power Part of the Ordinary Discourse? The Case of Ethiopian State of Emergency Declared on February 16

 

 

Introduction

In this piece, I will examine the legality of and intent induced the State of Emergency (SoE) declared on Feb. 16, 2018, in Ethiopia. Throughout, I will utilise legal and public choice analytical models. To do so, I will start by giving an overview of SoE as a general practice and under the 1995 FDRE constitution. I will then employ functional analysis to highlight the functions of SoE – mainly reassurance and existential rationales. Tied to the functional review, I will discuss the possibility of abuse of function and alternatives to control an abuse through ex-ante and ex-post monitoring mechanisms. In the fourth section, I will turn to the examination of a motive element that may induce declaration of SoE with a focus on benevolent intent and as a power-maximizing tool. Against these theoretical backdrops, under the fifth section I will diagnose the legality of and the rationale that induced the declaration of the current SoE. I would argue that SoE is an extraordinary power to be used in any but dire circumstances. The vaguer the condition for declaring an emergency and the weaker the check and balance of emergency process, the higher will be the risk of emergency power abuse. Further, its repeated reoccurrence sets a threat of normalization of SoE which is as much dangerous as the threat it is meant to mitigate.      

Continue reading
  11283 Hits

በክልል የተገደበው የመዘዋወር ነፃነት

 

 

1. የመዘዋወር ነፃነት አለም አቀፋዊ አንድምታው

የሰው ልጅ ሰው ሆኖ በመፈጠሩ ከሚያገኛቸው አያሌ የተፈጥሮ መብቶች ውስጥ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ የሰው ልጆችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት ከሐይማኖት፤ ከባህል እና ከሌሎች የተፈጥሮ ህግጋት ጀምርን ስንመለከተው ፅኑ መሰረት ያለው ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በአለማችን ታሪክ ይህ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት በአንዳንድ የታሪክ አጋጣሚዎች ላይ ተገድቦ የነበረ ቢሆንም በአብዛኛው ግን ሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብታቸው ሲከበር ቆይቷል፡፡ ይሄንን ተፈጥሮአዊ መብት በመጠቀም የተለያዩ የአውሮፓ ሰዎች አዲስ ግኝትን፤ የመካከለኛውና የሩቅ ምስራቅ ሀገሮች ደግሞ ንግድን በማጧጧፍ ለሀገራቸው እና ለአህጉራቸው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አበርክተዋል፡፡ ይህንን ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደ ማግና ካርታ (Magna Carta) አይነት ጥንታዊ ሰነዶች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብትን አውጀዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በታላቋ ሮም የነገሱ አብዛኛው ነገስታት ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነትን ሲያከብሩ መቆየታቸውን የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

ይሁን እንጅ አለማችን በታሪኳ ካጋጠሟት ጠባሳ ታሪክ በቀዳሚነት የሚጠቀሰው የሁለተኛው የአለም ጦርነት እና ከዚህ ጦርነት ጋር በተያያዘ ከተከሰቱ እጅግ አስከፊ የመብት ጥሰቶች መካከል ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት ይጠቀሳል፡፡ አንድ ችግር ሲፈጠር ለችግሩ መፍትሄ መስጠት ወይም መንገድ ማበጀት የሰው ልጅ ተፈጥሮአዊ ባህሪው በመሆኑ በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት የተፈጠሩ የመብት ጥሰቶችን በማስመልከት የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደው ነበር፡፡ ከተወሰዱ እርመጃዎች መካከል አለም አቀፍ የሰበዓዊ መብት ተቋማትን መመሰረትና አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሰነዶችም ማዘጋጀት ይጠቀሳሉ፡፡ በዚህም መሰረት በተቋም ደረጃ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሲቋቋም በሰብዓዊ መብት ሰነድ ደረጃ ደግሞ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌ (Universal Declaration of Human Rights) እና ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት (International Covenant on Civil and Political Rights) በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌ በአንቀፅ 13[1] ላይ በግልፅ ለመዘዋወር ነፃነት እውቅና የሰጠ ሲሆን የዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት ደግሞ በአንቀፅ 12 ላይ ተመሳሳይ ድንጋጌ አስቀምጧል፡፡ በተለይ ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት በአንቀፅ 12 ላይ በመርህ ደረጃ ይህ መብት ገደቦች የሌሉበት ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በህግ በተደነገጉ ቀድመ ሁኔታዎች አማካኝነት ሊገደብ የሚችልበት ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ከብሔራዊ ደህነት፤ ከህዝብ ሞራል እና ጤና ጋር የሚያያዙ ናቸው፡፡ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎችን መሰረት አድርጎ የሚወጣ ህግ ከአድሎ ነፃ የሆነ እና የትኛውንም ህዝብ በተለይ የሚጎዳበት አግባብ ሊኖር እንደማይገባው ይደነግጋል፡፡ በአጠቃላይ አለማችን አሁን በደረሰችበት የአእምሮ ማሰብ አድማስ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት የሰው ልጅ ከተሰጡ መሰረታዊ መብቶች ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ከመሆኑ አንፃር የአለማችን የህግ ሰዎችም ሆኑ ፖለቲከኞች በአስፈላጊነቱ ዙሪያ ሙሉ ለሙሉ ይስማማሉ ማለት ይቻላል፡፡ በመሆኑም በአለም አቀፍ የልማዳዊ ህግ መስፈርቶች መሰረት ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት የአለም አቀፍ የልማድ ህግነት ደረጃ ደርሷል ማለት እንችላለን፡፡ በመሆኑም ማነኛውም ሀገር፤ በሀገር ውስጥ ያለ አስተዳደራዊ ክልል እንዲሁም ማነኛውም መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ይህንን መብት የማክበር እና የማስከበር ግዴታ አለበት፡፡

Continue reading
  8406 Hits

በኢትዮጵያ በኢንተርኔት ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት እና ገደቡ

መግቢያ

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ለዲሞክራሲያዊ ማህብረሰብ መፈጠር የመሰረት ድንጋይ ነው፡፡ ይህ መብት በጣም ረጅም ጊዜ ያስቆጥረ የሰው ልጅ መብት ሲሆን በዘመናት መካከል በፈላጭቆራጭ ነገስታት እና መሪዎች ጫና ተደርጎበታል፡፡ ለአብነት ያህልም በጥንታዊ ባቢሎናዊያን የልዩነት ሃሳብ (being dissenter) መያዝ ወደ እቶን እሳት ያስጨምር እንደነበር ከመጽሃፈ ዳንኤል  ምዕራፍ 3 ንባብ መረዳት እንችላለን፡፡

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት የፍልስፍና መሰረቱ ከጥንት ግሪካዊያን ስልጣኔ ጋር አብሮ ይነሳል፡፡ በተለየም የዴሞክራሲ ታሪካዊ ከተማ በሆነችው አቴንስ የመናገር ነጻነት ዋጋ ህይዎትን እስከወዲያኛው ሊያስነጥቅ የሚችል ነገር ነበር፡፡ በዚህ ረገድ የሶቀራጥስ የፍርድ ችሎት ለዘመናት እንደ የመናገር ነጻነት ጥሰት ተደርጎ በድርሳናት ይወሳል፡፡ (አርሊን ሳክሶንሃውስ፡2006፡102)

በአውሮፓዊያን የዕውቀት ስልጣኔ (enlightenment period) ጫፍ በነካበት ወቅት የመናገር ነጻነት አምባገነን መንግስታትን በሃሳብ ለመሞገት የሚስችል መሳሪያ ነበር፡፡ ለምሳሌ:- ባሮን ሞንተስኩ የተባለ የፈረንሳይ ፈላስፋ የመንግስት ስልጣን ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፍፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ ተብሎ መከፈል እንዳለበት በጹሁፍ እና በቃል በማስተማሩ የማታ ማታ ሃሳቡ ተቀባይነት ሊያገኝ ችሏል፡፡ በኋላም እኤአ ከ 1789_1799 ዓ.ም በነበረው የፈረንሳይ አቢዮት የመናገር መብት የሰው ልጆች ትልቁ ነጻነት እንደነበር ታሪክ መዝግቦታል፡፡ በታላቋ ብሪታኒያ እና አሜሪካም የመናገር ነጻነት የሊብራል የፖለቲካ አስተሳሰብ እና ዴሞክራሲ እንዲያብብ በማስቻል ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ በተለይም እነዚህ አገራት ጆን ሚልተን፣ ጆን ስቱዋርት ሚልን ጨምሮ ጀምስ ማዲሰንን የመሰሉ ሃሳብን በነጻነት የመናገር መብት ተሟጋቾችን አፍርተዋል፡፡

ልክ እንደ ዘመነ ሶክራጥስ ሁሉ ዛሬም ሃሳብን በነጻ መግለጽ እንደ ጅማል ካሾጊ ህይዎትን እስክ ወዲያኛው ሊያስከፍል ይችላል፡፡ በአምባገነኖች ግፊት አገር እስጥሎ ስደተኛ ያደርጋል፤ ለእስር ብሎም ለተለያዩ እንግልቶች ይዳርጋል፡፡

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ሲባል ግለሰቦች ሃሳባችውን መግለጽ፣ መረጃ ማግኘት፣ መጠየቅ እንዲሁም ለሌሎች የማካፈል መብትን ጨምሮ በፈለጉት መንገድ ማለትም በጽሁፍ፣ በንግግር፣ በምልክት፤ በኢንተርኔት ወይም በሌላ መንገድ በመጠቀም መልዕክት የማስተላልፍ መብት ነው፡፡

Continue reading
  12004 Hits

የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ሕገ-መንግሥታዊነት

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ መንግሥት የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽንን የሚያቋቁም አዋጅ ማፅደቁ ይታወቃል፡፡ አዋጁ በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ የጦፈ ክርክርን አስነስቶ በ33 ተቃውሞ እና በ4 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ ቢፀድቅም በፓርላማ ውስጥ ለአዋጁ ድምፅ ከነፈጉ የሕዝብ ተወካዮች ጀምሮ እስከ ክልል መንግሥታት ድረስ ሰፊ ተቃውሞን አስተናግዷል፡፡ ለተቃውሞው መነሻ የሆነው ዋነው ጉዳይ የማንነትም ሆነ በክልሎች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶችን መፍታት የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የክልሎች ሥልጣን ሆኖ ሳለ ሌላ ተቋም የማቋቋም አስፈላጊነት እና ሕገ መንግሥታዊነት ጥያቄ ነው፡፡

ለእነዚህ ጉዳዮች በሕግ አግባብ መልስ ለመስጠት ሁለት ጉዳዮችን በጥልቀት ማገናዘብ ይጠይቃል፡፡ አንደኛው እና መሠረታዊው ጉዳይ በሕገመንግሥቱ እና በሥራ ላይ በነበሩ ሕጎች  መሠረት የማንነት እና ራስን የማስተዳደር ጥያቄዎች እንዲሁም በክልሎች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶች የሚፈቱበት ሥርዓት ምን እንደሆነ መፈተሸ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ለኮሚሽኑ የተሰጠውን ሥልጣን እና ተግባር ከሕገ-መንግሥቱ ጋር በንፅፅር አይቶ ሕገ መንግሥታዊነቱን መመርመር ነው፡፡

የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎች

በሕገ መንግሥቱ መሠረት የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን የመፍታተት ሥልጣን በመሰረታዊነት የተሰጠው ለክልሎች (ምክር ቤት) ነው፡፡ ነገር ግን የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት መሆኑ በሕገ መንግሥቱ ከመደንገጉም በላይ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 እንደተቀመጠው ክልሎች ለቀረበላቸው ጥያቄ በአንድ ዓመት ውስጥ አጥጋቢ መልስ ካልሰጡ ጥያቄው በይግባኝ መልክ ለፌዴሬሽ ምክር ቤት ቀርቦ የመጨረሻ ውሳኔ ማግኘት ይችላል፡፡

በመሠረቱ በማንነት እና ራስን በራስ በማስተዳደር ጥያቄዎች መሀል ምን ልዩነት እና አንድነት እንዳለ በግልፅ ያስቀመጠ ሕግ የለም፡፡ በሕገ መንግሥቱና በሌሎች ሕጎችም ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ እንጂ ‹የማንነት ጥያቄ› በሚል አገላለፅ የተቀመጠ መብትም ሆነ ሥርዓት የለም፡፡ ከዚህ ባለፈም በአንዳንዶች ዘንድ በክልሎች መካከል የሚነሱ የወሰን አለመግባባቶች እና በማንነት ጥያቄዎች መካከል ያለውን ልዩነት ያለመረዳት ስህተት ይስተዋላል፡፡ በዚህ ላይ የሚነሱ ክፍተቶች እና አከራካሪ ጉዳዮች በሌላ ሰፊ ጽሑፍ ቢታዩ ተመራጭ ስለሆነ ዝርዝሩን በመተው ወደ ቀጣዩ ጉዳይ እናልፋለን፡፡

Continue reading
  10120 Hits

የፌዴሬሽኑ አባል ክልሎች የፌዴራሉን መንግሥት ሕጎች አልፈፅምም ማለት ይችሉ ይሆን?

መግቢያ

የፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 53 መሠረት በተቋቋመ ወዲህ ላለፉት 24 ዓመታት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከ1100 በላይ አዋጆችን ያወጣ ሲሆን ከእነዚህም አዋጆች ውስጥ በምክር ቤቱ በሚገኙ የገዢው ፓርቲ አባላት መካከል ሞቅ ያሉ ክርክሮችና የልዩነት ሃሳቦች ያስተናገዱ በጣት የሚቆጠሩ አዋጆች መሆናቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ሞቅ ያሉ ንትርክ አዘልና የልዩነት ሃሳቦች ከተንፀባረቁባቸው ሕጎች መካከል ለአብነት ያህል በሚንስትሮች ምክር ቤት ከየካቲት 06 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ተፈፃሚነት የነበረውንና ለሁለተኛ ጊዜ በሚኒስትሮች ምክር ቤት አዋጅ ቁጥር 2/2010 የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቀባይነት እንዲያገኝ በቀረበ ወቅት የተደረገው እልህ አስጨራሽ ክርክር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡

በተመሳሳይ መልኩ የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1101/2011 የፀደቀባት ሁኔታ የጋለ ክርክርን ያስተናገደ ነበር፡፡ የፌዴራሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 11 ቀን 2011 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የኮሚሽኑን ማቋቋሚያ አዋጅን በ33 ተቃውሞ በ4 ድምፅ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል፡፡ በዚህ አዋጅ ላይ የተደረገው ክርክርና የሰላ ሂስ በምክር ቤቱ ባሉአባላት ብቻ ሳይወሰን ከምክር ቤቱ ውጪ ባሉ የፖለቲካና የሕግ ሊሂቃን መካከል የከረረ ክርክርና ትችት ሲያስተናግድ ሰንብቷል፡፡

የኮሚሽኑን ማቋቋሚያ አዋጅ ሕገ-መንግሥታዊነቱንና ሥልጣኑን በተመለከተ የሚቀርበው ድጋፍና ትችት በግለሰቦች ደረጃ ብቻ የቀረ ሳይሆን የትግራይ ክልል ምክር ቤት በጥር 18 ቀን 2011 ዓ.ም ባካሄደው 5ኛ ዓመት 14ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይም የመከራከሪያ አድማስ ሆኖ በአዋጅ አፈፃፀም ላይ የክልል ምክር ቤቱን የውሳኔ ሃሳብ እስከማሰጠት ደርሷል፡፡

የዚህ ጽሑፍ መነሻ ሃሳብም የትግራይ ክልል ምክር ቤት በኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ በሰጠው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ሲሆን በዚህም አግባብ የክልሉ ምክር ቤት የፌዴራሉን መንግሥት ሕጎች አልተገብርም ማለቱን ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንፃር ያለውን ውጤት እና የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ሥልጣንና ተግባርን አጠቃላይ እንድምታ የምንዳስስ ይሆናል፡፡

Continue reading
  11064 Hits

ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ

አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡

የዚህ አጭር ጽሑፍ መነሻ ነጥብም በሕግ ማስከበር ሰበብ ለረዥም አመታት ከማህበረሰቡ ጋር በመቀላቀል ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ንብረት ያፈሩ ዜጎች ላይ በሕገ ወጥነት ሰበብ እየተወሰደ ያለውን ከገዛ ቤታቸውና ንብረታቸው የማፈናቀል እርምጃን በተመለከተ ዜጎች መብቶቻቸውን በሕግ አግባብ እንዴት ማስከበር እንዳለባቸው የሚያሳይ ፍኖተ ሕግ ነው፡፡

የህጉን ዝርዝር ነጥብ ከመመልከታቸን በፊት አሁን መሬት ላይ ያለው እውነትን በጨረፍታ ለመመልከት መሞከሩ ተገቢ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ በቅርቡ በአዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች መካከል የሰበታ ከተማ አስተዳደር፤ የቡራዩ ከተማ አስተዳደር፤ የለገጣፎ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር የከተሞቻቸውን የማስተር ፕላን ጋር ተቃራኒ የሆኑ እንዲሁም ቀድሞ ካሳ የተከፈላቸው እና በሕገ ወጥ መንገድ ከመንግስት እውቅና ውጭ ንብረት ያፈሩ ወይም በተለምዶ ወቅታዊ አጠራሩ ሕገ ወጥ ግንባታዎችን  አጭር የማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ነዋሪዎቹ ለዓመታት ይኖሩበት የነበረውን በጉልበታቸውና በጥሪታቸው ያፈሩትን ሃብቶቻቸውን በሃይል ድርጊት እንዲፈርስ በማድረግ በተጨባጭ ዜጎች ከሃብት ንብረታቸው እንዲፈናቀሉ መደረጉ ለብዙ ቅሬታ መነሻ ነጥብ ሆኖ መገኘቱ ነው የዚህ ጽሑፍ መነሻ ነጥብ፡፡ በመሆኑም ዜጎች ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈጸምባቸው በምን አግባብ መብቶቻቻውን ማስከበር እንደሚችሉ ከኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት እና ከአዋጅ ቁጥር 721/2004 ጋር በማመሳከር ረጂ ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውን ነጥቦች ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡  

በቅድሚያ የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 25 መሰረት ማንኛውም ሰው ልዩነት ሳይደረግበት በሕግ እኩል ያልተነጣጠለ እና አድሏዊ ባልሆነ መልኩ ጥበቃ እንደሚደረግለትና  እኩልና ተጨባጭ የሕግ ዋስትና የማግኘት መብት እንዳላቸው በማያሻማ ቋንቋ የማይገረሰሰ ሰብዓዊ መብት እንደሆነ ደንግጎ ይገኛል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ከጉዳያችን ጋር ተያያዥነት ባለው መልኩ በዚሁ ሕገ መንግስት አንቀፅ 32 ላይ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በመረጠው የሃገሪቱ አካባቢ የመዘዋዋርና የመኖርያ ቤት የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሃገር የመውጣት ነፃነት እንዳለውና በአንቀጽ 40/7ም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው በማለት እርስ በርስ ተመጋጋቢ እና ተደጋጋፊ በሆነ መልኩ የዜጎችን ንብረት የማፍራትና በሃገራቸው በነፃነት የመዘዋወር ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በዝርዝር ይጠቅሳል፡፡

Continue reading
  10224 Hits
Tags: