የማይደፈረውን ፍርድ ቤት መድፈር

በአንጌሳ ኢቲቻ የተጻፈውን ‹‹ችሎት መድፈር፡- ሕጉና የአሠራር ግድፈቶች›› የሚለውን ሳነብ እ.አ.አ በታኅሣስ 2013 በተመሳሳይ ርዕስ የጻፍኩትን ለአንባብያን ለማካፈል ወደድኩ፡፡ በዚህ ጽሑፌ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ማለት ነው? የኢትዮጵያ ሕግ ስለ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ይላል? የሕጉ ዓለማስ ምንድነው፣ የወንጀሉ አወሳሰን ልዩ ባህርይስ እንዴት ይታያል፣ በአፈጻጸም የሚታዩ ችግሮች ምንድናቸው የመሚለውን እዳስሳለሁ፡፡

  11932 Hits

አንዳንድ ምልከታዎች ስለ መገናኛ ብዙኃን እና የሐሰት ዘገባዎች

ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እጅግ መሠረታዊ መብት ከመሆኑ የተነሳ የተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ ጥበቃ የሚያደርጉለት ሲሆን በአለማችን ላይ በአንባገነንነታቸው የሚታወቁ መንግሥታት ሰይቀሩ መብቱ ሳይሸራረፍ በሀገራቸው እንደሚጠበቅ ይከራከራሉ። በዚህ ጽሑፍ ሀሳብን በነፃነት መግለጽ መብት በሰፊው ከሚተገበርበት ስለ መገናኛ ብዙኃን መብት እንመለከታለን። በመጀመሪያው ክፍል የመገናኛ ብዙኃን ለምን የሐሰት ዘገባዎችን ይሠራሉ በተለይም በመንግሥት ይዞታ ሥር የሚገኙ ወይም ዋነኛ የፋይናንስ ምንጫቸው በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ከመንግሥት የሆነ የሚለውን እናያለን። በመቀጠል የመገናኛ ብዙኃን የሰሩት ፕሮግራም እውነታን ያዘለ ሆኖ ሳለ የእርምት ወይም መልስ የመስጠት መብት ያለው አካል ሐሰተኛ ማስተባበያ ይዞ ቢቀርብ የማስተላለፍ ግዴታ አለባቸው ወይስ የለባቸውም የሚለውን እንመለከታለን። በመጨረሻም ነፃ ሚዲያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ከሀገራችን ሕጎች አንፃር አጭር ዳሰሳ እናካሔዳለን።

  9323 Hits
Tags:

ዳኛ  እግዜር! ዳኛ ከችሎት ይነሳ!

ሀገሬው የዳኝነትን ሥራ (ፍትሕ መስጠት) ሃሳባዊ በማድረግ ደረጃውን ከፍ ሲያደርገው “ዳኛ እግዜር!” ይላል፡፡ ከሳቴ ብርሃን የአማርኛ መዝገበ ቃላትም ዳኛ ማሪያም! ተሙዋጋች በዳኛ ፊት ቆሞ ሲአመለክት ዳኛ እግዚአብሔር! ያሳይህ ዳኛ ማርያም ወይም ሲሙአገት ጭብጥ የያዘውን አስመስካሪውን ዳኛ የምስክሮቹን ቃል ለማሳሰብ ተዘከረኝ ዳኛ ማሪያም ይላል በማለት ይገልፀዋል፡፡ እንደ ፕልቶ ያሉ ሃሳባውያን (idealist) ፈላስፎች “ፍትሕ” ሃሳባዊ ተፈጥሮ ያለው፣ ከሰብዓዊ ባህርይ ውጪ የሆነ እና አሁን ባለው ዓለም (physical world) ሳይሆን በጊዜ እና በቦታ ባልተገደበው ሃሳባዊ ዓለም የሚገኝ እንደመሆኑ ስሙ ብቻ የሚታየውን ሃሳብ ቅርፅ ወዳለው ድርጊት በሕግ መልክ ሆነ በሌላ ዘዴ ወደ ዚህኛው ዓለም ሊመልሱት እና ሊፈፅሙት የሚችሉት እውነተኛው ሃሳብ የሚታያቸው ሰዎች ናቸው ይላል፡፡ እንግዲህ ሀገሬው “ዳኛ እግዜር” ሲል በፍትሕ ላይ ሃሳባዊ መሆኑ ነው፡፡ “ፍትሕ ከፈጣሪ  ነው” ብሎ ለሚያምን ማህበረሰብ ሰው በፈራጅነት ቦታ ቁጭ ብሎ ሲያገኘው  በአገረኛ ዘዬ ኧረ! ዳኛ እግዜር! ቢል አይገርምም፡፡ ሌላው ሀገሬው በፍትሕ ላይ ሃሳባዊ ለመሆኑ መገለጫ የሚሆነው ለዳኛ ሲሰጠው የነበረው ልዩ ቦታ ነው፡፡ የአንድ ማህበረሰብ ወግ እና ሥርዓት የሚቀዳው ካለው አካባቢያዊ የእምነት እና አስተሳሰብ መሠረት አድርጎ ነው፡፡ ለማሳያ ያህል  ከፍትሐ ነገስቱ አንድ ነገር አንጠልጥለን እንውጣ፡፡

  12973 Hits

በጣልቃ ገብ እና የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅኝ  አቤቱታ ላይ የዳኝነት ይከፈላል?

ለዚህ ጽሑፍ  መነሻ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 አንድ ሰው በተጀመረ ክርክር መብቴ ይነካል፤ ወደ ክርክሩ ጣልቃ ገብቼ ልከራከር ብሎ ሲጠይቅ እና በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418 ለፍርድ ማስፈፀሚያ የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ይለቀቅልኝ በማለት አቤቱታ ሲያቀርብ የዳኝነት ይከፈላል ወይስ አይከፈልም የሚለው ጉዳይ ነው፡፡

  14154 Hits

የእንደራሴነት ሕግ (Agency Law) ዋና ዋና ነጥቦች

ሰዎች ኑሮአቸውን ስኬታማ ለማድረግ በሚፈጽሙት የእለት ተእለት ተግባራቸው ከሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎች ጋር ዘርፈ ብዙ መስተጋብሮችን የሚፈጽሙ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይሁንና እነኚህን መስተጋብሮች  በተለያዩ ምክኒያቶች በራሳቸው ለመፈጸም የማይችሉ በሆነ ጊዜ ሥራዎችን ሌላ ሰው እንዲያከናውንላቸው ፍላጎት ሊያድርባቸው እንደሚችል የሚያሻማ አይደለም፡፡ በዚሁ መሠረት ይህንኑ ሥራቸውን ማን፣ መቼ፣ በምን ሁኔታ እና በድካም ዋጋ ክፍያ ወይም ያለ ክፍያ  ሊሠራላቸው እንደሚገባ የመወሰን ነጻነት ሊኖራቸው የተገባ ነው፡፡  

  13434 Hits
Tags:

አላግባብ/በስህተት የተከፈለን የጡረታ አበል ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የሚያስቀረዉ የይርጋ ዘመን ምን ያህል ነዉ?

የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በሰበር ችሎት ዉሳኔዎች ቅጽ 14 መግቢያ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፤ “ለተመሣሣይ ጉዳዮች በጣም የተራራቁ ዉሣኔዎችን በመስጠት ይታይ የነበረዉን ችግር በመቅረፍና የዉሣኔዎችን ተገማችነት በማረጋገጥ ረገድ የሰበር ዉሣኔዎች አስገዳጅ መሆን ከፍተኛ ዉጤት አስገኝቷል ማለት ይቻላል፡፡ አልፎ አልፎ በዉሣኔዎች ጥራትና ስርጭት ሊታዩ የሚችሉ ችግሮች ሥርዓቱ እየተጠናከረ ሲሄድ የሚፈቱ ሲሆን አነዚህን ችግሮች ለማቃለል እኛም ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ጥረታችን ሊሳካ የሚችለዉ በዉሣኔዎቹ ላይ በሕግ ምሁራንና ባለሙያዎች ገንቢ የሆኑ ትችቶችና አስተያየቶች ሲቀርቡ ነዉ”፡፡ እኔም ይህን ግብዣ በመቀበል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎት ሕዳር 21 ቀን 2005 ዓ.ም. በሰጠዉ ዉሳኔ ላይ ትችቴን ከዚህ በመቀጠል አቀርባለሁ፡፡ ዉሳኔዉ የተሰጠዉ በማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ እና ታዬ አበራ መካከል ባለዉ ክርክር በሰበር መዝገብ ቁጥር 72341 ነዉ፡፡ በዚህ መዝገብ ከተነሱት ዋነኛ ጉዳዮች ዉስጥ፤ አላግባብ የተከፈለ ጡረታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይ፤ ከታገደስ የይርጋ ዘመኑ ምን ያህል ነዉ የሚሉት ይገኙበታል፡፡

  12592 Hits

ኢትዮጵያ ውስጥ በሚሠሩ ፊልሞች ላይ የሚታዩ የሕግ ግንዛቤ ክፍተቶች

ፊልሞችን ሰርቶ ለሕዝብ ማቅረብ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29 ላይ የተቀመጠው ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት አንደኛው መገለጫ ነው፡፡  ሀሳብን የመግለፅ መብት ከመንግሥት ገደብ (Limitation) ሊጣልበት የሚችለውም ውስን በሆነ ምክንያት እንደሆነ ይሄ ሕግ መንግሥት የሚያስቀምጠው ጉዳይ ነው (አንቀጽ 29/6ን መመልከት ይቻላል)፡፡ አዋጅ ቁጥር 533/2007 እና ከዛ በፊት የወጡ ሕጎችም ትልቅ ጥበቃ ሊደረግለት የሚገባውን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ሊገደብ የሚችልበትን አግባብ ያስቀምጣሉ፡፡ ሀሳብን የመግለፅ መብት በሕግ የሚገደበውም ሦስት መሠረታዊ ፍላጎቶችን (Interests) ለመጠበቅ ሲባል ብቻ ነው፡፡ እነዚህም፡-

  11854 Hits
Tags:

ሕግ የማታከብረው ከተማ

በከተማችን ሰማይ ላይ የሰፈረ መንፈስ አለ የሆነ ህጻኑን ወጣቱን አዛውንቱን የሚፈታተን መንፈስ፡፡ በራዲዮ ቢራ፣ በቴሌቭዥን ቢራ፣ በቢልቦርዶች ገፅ ላይ ቢራ ሆኗል ከተማው፡፡ ዛሬ ዛሬ ቢሮ ከሚለው ስም ይልቅ ቢራ የሚለውን ስም መስማት የተለማመደ ሆኗል፡፡ እኔም በእለት ተእለት እንቅስቃሴም ውስጥ በሁለት ነገሮች እርግጠኛ ነኝ ከእሁድ በስተቀር ቢሮ እንደምገባና አንድ የቢራ ማስታወቂያ ጆሮየ እንደሚሰማ፡፡ ከወዳጅ ዘመዶቼ ይልቅ አዲሱ ዓመት መልካም እንዲሆንልኝ አብዝተው የተመኙልኝም የቢራ ማስታወቂያዎች ናቸው፡፡ ቢራ ስትጠጣ አዲሱ ዓመት የሰላም የጤና የብልፅግና ይሆንልሀል ዓይነት ፉገራ እየፎገሩኝ፡፡ ይህን ያህል ቢራ የሕይወታችን ገፅታ ሆኗል፡፡ ስለቢራ ላለመስማት ብር ብሎ ከመጥፋት ውጭ አማራጭ የለም በመዝናናታችን መኃል፣ በመንገዶቻችን ዳርቻ፣ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎቻች ቢራ አለ፤ ቢራ መኖሩ አይደለም ችግሩ፣ ችግሩ ቢራ አብዝቶ መኖሩና እየተነገረበት ያለው መንገድ ነው፡፡ ቢራ የማኅበራዊ የሥነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይታችን ጋሬጣ ሊሆነ በሀገሪቱ ሰማይ ላይ አንዣቧል፡፡

  11852 Hits

ስለ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች መልስ የሚሹ ጉዳዮች

በተደራጀ እና በብሔራዊ ሕግ ዕውቅና አይሰጣቸው እንጂ በኢትዮጵያ የሸሪኣ ሕግን መሠረት በማድረግ ውሳኔ መስጠት የቅርብ ታሪክ አይደለም፡፡ በታወቀ ሁኔታ እና በመንግሥት ድጋፍ የሸሪኣ ፍርድ ቤቶች የተቋቋሙት ግን በ1934 ዓ.ም. ነው፡፡ ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ሕጉ ከሁለት ዓመት በኋላ ተሻሻለ፡፡ ቀጥሎም አገሪቱ በፌደራል ሥርዓት መተዳዳር ከጀመረች በኋላ በ1992 ዓ.ም. እንደ አዲስ የፌደራል ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች ተቋቋሙ፡፡ በፌደራል ብቻ ሳይወሰኑ በክልሎቹም እንዲሁ ተቋቋሙ፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋና መሠረቱ አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገ መንግሥት ነው፡፡ በአንዳንድ ክልሎች፣ ከመደበኛው ፍርድ ቤት ጎን ለጎን በችሎትነት ሲቋቋሙ በፌደራል ደረጃ ግን ራሳቸውን ችለው የመጀመሪያ ደረጃ፣ ከፍተኛ እና ጠቅላይ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች በመባል ተቋቁመዋል፡፡

  16402 Hits

የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸውና የማይከፈልባቸው ግብይቶች

መንግሥት ገቢ ከሚሰበሰብባቸው ምንጮች መካከል የቴምብር ቀረጥ አንዱ ነው፡፡ የቴምብር ቀረጥ ቀጥተኛ ያልሆነ ታክስ ሲሆን፣ የሚሰበሰበውም በተወሰኑ ሰነዶች ላይ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል በማድረግ ነው፡፡ በአገራችን የቴምብር ቀረጥ የተጣለው ስለ ቴምብር ቀረጥ አከፋፈል በወጣው አዋጅ ቁጥር 110/90 መሠረት ነው፡፡ የዚህ አዋጅ አፈጻጸም በተለያዩ ባለድርሻ አካላት መካከል ያለው አሠራር ተመሳሳይ አይደለም፡፡ በተግባር በሰነዶች የተለያዩ ግብይቶች (Transactions) የሚፈጸሙ ሰዎች፣ የአገር ውስጥ ገቢ ሠራተኞች፣ ባንኮች፣ ፍርድ ቤቶች ወዘተ የየራሳቸው የአዋጁ አረዳድ አላቸው፡፡ የልዩነቱ ምንጭ አዋጁን ካለማወቅ፣ ከአዋጁ ድንጋጌዎች ይልቅ በልማድ መሥራት፣ እንዲሁም የአዋጁን ክፍተት የሚሟሉ መመርያዎችን አለማወቅ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች አመልክተዋል፡፡ እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ የአዋጁ አፈጻጸም የሕግ አውጪውን መንፈስ እንዲከተል ማስቻል የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ነው፡፡

  21240 Hits
Tags: