ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ያላቸው ደረጃ

ስለዓለም አቀፍ ሕግ በአጭሩ

ዓለም አቀፍ ሕግ በሉዓላዊ አገሮች መካከል ያለን ግንኙነት ወይም በአገሮችና እንደተባበሩት መንግሥታት ያሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል ያለን ግንኙነት የሚገዛ የሁሉ አቀፍ ደንቦች እና መርሆዎች ሥርዓት ነው። በሌላ አነጋገር «International law is the universal system of rules and principles concerning the relations between sovereign States, and relations between States and international organizations such as the United Nations» የሚል ትርጉም ተሰጥቶት እናገኘዋለን። ቀደም ባሉት ጊዜያት በዓለም አቀፍ ሕግ እና በየሐገሩ በሚገኙ ዜጎች፣ ሉአላዊ ባለሆኑ አካላት (Transnational Corporations) እና መንግሥታዊ ባለሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች (International Non-Governmental Organization) ቀጥተኛ ግንኙነት ያለነበረ ቢሆንም አሁን አሁን ግን ይህ የታሰበው ቀጥተኛ ግንኙነት በስፋት እየታየ መሆኑን ዓለም አቀፍ ምሁራንን እያስማማ ነው።

  19373 Hits

Justification of Excise Tax in General

Excise taxes are an example of what have been traditionally called indirect taxes: taxes that are imposed on a transaction rather than directly on a person or corporation. Excise taxes are narrow-based taxes, as compared with broad-based taxes on consumption such as a general sales tax, a value-added tax, or an expenditure tax. Excise taxes can be collected at various stages, including the point of production, the wholesale level, or the retail level. They are also known as selective sales taxes or differential commodity taxes.

  22565 Hits

የግል አቤቱታ የማቅረብ መብት በጠቅላላው

የሥነ-ሥርዓት ሕግ ሰዎች መሠረታዊ የሆኑ የፍትሕ አቤቱታዎች ሲቀርቡ የሚመሩበትን እና መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት የሚወስኑበትንና ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚያሳይ ጽንሰ ሀሳብ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕግ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በምንና እንዴት ባለ አኳኋን ወደ ተግባር ሊፈፀሙ እንደሚችሉ የሚዘረዝር የሕግ ክፍል ነው። የእነዚህን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች ይዘትና አይነት ተንትኖ የሚያቀረበው የሕግ ክፍል መሠረታዊ ሕግ (Substantive Law) ተብሎ የሚጠራ ነው። መሠረታዊ ሕግ የሰው ልጆችን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በግልፅ የሚደነግግ በመሆኑ ጠቀሚታው ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል። ይሁን እንጅ እንዚህ ዝርዝር መብቶችና ግዴታዎች በተግባር ተፈፃሚ እንዲሆኑ ካልተደረገ የመኖራቸው ጉዳይ ትርጉም የለሽ ይሆናል ማለት ነው። እነዚህ መደበኛና ልዩ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች እንዲፈፀሙ የማድረጉ ሐላፊነት የሥነ-ሥርዓት ሕግ ቢሆንም ውጤታማ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከሌለ ግን መብቶችንና ግዴታዎችን የማስፈፀሙ ዓላማ እረብ የለሽ ይሆናል። ለዚህም ነው የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከመሠረታዊው ሕግ ባላነሰ አስፈላጊና ጠቃሚ ነው የሚባለው።

  21014 Hits

Letters of Credit in General

Letter of credit transactions have been developed since the Middle Ages in connection with the trade of goods at the international level. Individuals and companies have found themselves dealing with partners of whom they know little, located in distant countries with often insecure political and economic situations. Furthermore, the dynamism of the economy creates a need for financing that requires a guarantee of payment at a time and for an amount that must be certain. Diversity in geographical nature, weather, climate, production system, and globalization in culture and fashion has made the countries dependent on each other for the daily necessities. Similarly, one continent is largely dependent on the products of other continents. In addition, diversity in human appetite and attitude, unequal development of technology, desire for luxury, and the development of communication systems and tale-communication revolutionarily increase the necessity of transnational, transcontinental business activities.

  22061 Hits

ስለቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) ፍርድ ቤት ተልዕኮ፣ ሥልጣን እና ተግባር

በዘመናዊ አሠራር የወንጀል ጉዳይን እንዲከታተል የተቋቋመ እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለፍርድ ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዩች አይነትና ብዛት ለመለየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ይቀይስለታል፡፡ ይህ እንዲሆን የሚያሰፈለገውም በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በሚከሰሰበትና ለፍርድ በሚቀርብበት ጊዜ ብዙ ችግር ሊገጥመው እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ በወንጀል ተግባር ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ ሰው የሚደርስበት የማሕበራዊና የኢኮኖሚያዊ ቀውስ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ አይነቱ ከባድ ጉዳት ሊደርስ የሚገባው በእርግጥ ወንጀል በሰሩና ወንጀል ለመስራታቸውም የማያጠራጠር ማስረጃ በቀረበባቸው ሰዎች ላይ መሆን አለበት፡፡ አንድን ሰው ወንጀል ሰርተሃል ብሎ መክሰስና በማሕበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለውን ክብር ዝቅ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ክሱን በማስረጃ ማረጋገጥና ተከሣሹን ጥፋተኛ ማስደረግ ግን በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ በማስረጃ ሊረጋገጡ የማይችሉ ወንጀሎች በተቻለ መጠን በአጭሩ መቋጫ እንዲያገኙ ማድረግ የመንግሥት ሃላፊነት ነው፡፡

  16290 Hits

ሕገ መንግሥታዊ የዋስትና መብትን በመተርጎም በኩል ስለታየው ችግር

ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን ስምምነት& ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሕግጋት እና በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የተካተቱት ሥነ ሥርዓታዊ መብቶች መሠረታዊ ዓላማ መርማሪ አካላት ያለበቂ ምክንያትና ሕጋዊ ሥርዓት የአንድን ሰው የነጻነት መብት እንዳይጥሱ ዋስትና እና ጥበቃ መስጠት ነው፡፡ የብዙ አገሮች ሕገ መንግሥት የአንድ ሰው በሕይወት የመኖር& የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት ከሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክቡርነት የመነጩ ሊደፈሩና ሊገሰሱ የማይችሉ መብቶች መሆናቸውን ያረጋገጣሉ@ መሠረታዊ መብቶቹ ተግባር ላይ እንዲውሉ ጥረት የሚደረግ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ በሌላ በኩል የእነዚህን መብቶች አፈፃፀም የሚሸረሽሩ ወይም ዋጋ የሚያሳጡ የተለያዩ የወንጀል ድርጌቶች በዓለም ውስጥ በየደረጃው በስፋት ሲፈፀም ማየትና መስማት የተለመደ ሆኗል፡፡ ይህ የማይጣጣም ሁኔታ ከልዩ ልዩ የጥቅም ግጭቶች& ከአመለካከት ልዩነት& ካለመቻቻልና ከመሣሰሉት መንስዔዎች የሚመነጭ ሊሆን ይችላል፡፡

  18079 Hits