ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ያላቸው ደረጃ

 

1.    ስለዓለም አቀፍ ሕግ በአጭሩ

ዓለም አቀፍ ሕግ በሉዓላዊ አገሮች መካከል ያለን ግንኙነት ወይም በአገሮችና እንደተባበሩት መንግሥታት ያሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል ያለን ግንኙነት የሚገዛ የሁሉ አቀፍ ደንቦች እና መርሆዎች ሥርዓት ነው። በሌላ አነጋገር «International law is the universal system of rules and principles concerning the relations between sovereign States, and relations between States and international organizations such as the United Nations» የሚል ትርጉም ተሰጥቶት እናገኘዋለን። ቀደም ባሉት ጊዜያት በዓለም አቀፍ ሕግ እና በየሐገሩ በሚገኙ ዜጎች፣ ሉአላዊ ባለሆኑ አካላት (Transnational Corporations) እና መንግሥታዊ ባለሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች (International Non-Governmental Organization) ቀጥተኛ ግንኙነት ያለነበረ ቢሆንም አሁን አሁን ግን ይህ የታሰበው ቀጥተኛ ግንኙነት በስፋት እየታየ መሆኑን ዓለም አቀፍ ምሁራንን እያስማማ ነው።

ይሁን እንጂ ዓለም አቀፋዊ የሆነ ማዕከላዊ ሕግ አውጭ ባለመኖሩ፣ አለፎ አልፎ ከሚታዩት በስተቀር ዓለም አቀፍ ሕግን ውጤታማና ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲከበር የሚያደርጉ የእርምጃ ዘዴዎች ባለመጎልበታቸው፣ እራሱን የቻለ የተጠናከረ ማዕከላዊ አስፈጻሚ አካል ጎልቶ አለመታየቱ (የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ሳይዘነጋ መሆኑ ይታወቃል) ፣ ክርክሮችን ተቀብሎ እልባት የሚሰጠው ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤትም ስራውን የሚያከናውነው እና ችሎት የሚቀመጠው አለመግባባት የታየባቸው አገሮች በራሳቸው ፍቃደኝነት ጉዳያቸውን ሲያቀርቡለት እንጂ አስገድዶ የማስቀረብ ሥልጣኑም ሆነ ተቋማዊ አደረጃጀት የሌሉት መሆኑ እና ዓለም አቀፍ ሕግ በዓለም ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ በሆኑ አገሮች ጥቅምና አምሳል የተፈጠረ በመሆኑ እና አፈፃፀሙም በእነሱ ተጽዕኖ ሥር በመውደቁ ፍትሃዊነቱ አጠያያቂ ነው፣ የደሃ ሐገሮችን ጥቅም አያስጠብቅም የሚሉ ትችቶችን ወ.ዘ.ተ. ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ዓለም አቀፍ ሕግ የሚባል ነገር እንደ ሕግ የመቆም ብቃት የለውም የሚሉ ወገኖች እየበረከቱ መጥተዋል። በተለይ የሕግ መሠረታዊ ባህሪ ነው ተብሎ የሚታሰበውን የአስገዳጅነት ተፈጥሮ አልተላበሰም በሚል የሕግ ዋጋ የለውም እያሉ ክፉኛ ያብጠለጥሉታል።  ሌሎች ደግሞ እንደ ሕግ ባለመከበሩና በመጣሱ ምክንያት ብቻ ሕግ ከመሆን የሚያግደው ነገር የለም ባይ ናቸው። እንደዚያም ከሆነ ብሄራዊ ሕጎችስ በተደጋጋሚ ሲጣሱ ይታዩ የለምን? ሲሉ በአጽእኖት ይጠይቃሉ፣ እናም የዓለማችን ግንኙነት እየሰፋ በመጣበት በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፍ ሕግን አሳንሶ መመልከትም ይሁን ጭራሽ እልውናውን መፈታተን እውነታን ያላገናዘበ ድምዳሜ ነው ሲሉም ትችት ያቀርባሉ።   

ዓለም አቀፍ ሕጎች በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ልንመድባቸው እንችላለን። እነሱም ዓለም አቀፋዊ የመንግሥት ሕግ (Public International Law) እና ዓለም አቀፋዊ የግል ሕግ (Private International Law) በማለት ሲሆን ዓለም አቀፋዊ የመንግሥት ሕግ በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ ራሳቸውን በቻሉ ነፃ እና ሉአላዊ አገሮች መካከል የሚፈጠረውን የሁለትዩሽ ወይም ከዚያ በላይ ግንኙነቶች የሚገዛና የሚቆጣጠር ሕግ ነው። በሌላ በኩል ዓለም አቀፋዊ የግል ሕግ በፍትሐብሄር ጉዳዩች ዙሪያ የሚፈጠሩ ግንኙነቶች እና አለመግባባቶች በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ አገሮች ዜጎችን በተፎካካሪነት ያሳተፈ ሲሆን አልያም የሌሎች አገር ተወላጆች ንብረት በአንዲት አገር የሚገኝ ከሆነ እንዲሁም የውጭ አገር ዜጎች አንዳንድ የፍትሐብሄር ድርጌቶችን ለምሳሌ ውርስ፣ ውል፣ ከውል ውጭ የሚያስጠየቁ ኩነቶችን የፈፀሙ እንደሆነ አለመግባባቱ መፍትሄ የሚያገኘው በዓለም አቀፍ የግል ሕግ አማካኝነት ነው።   

Continue reading
  16703 Hits

Justification of Excise Tax in General

 

Excise taxes are an example of what have been traditionally called indirect taxes: taxes that are imposed on a transaction rather than directly on a person or corporation. Excise taxes are narrow-based taxes, as compared with broad-based taxes on consumption such as a general sales tax, a value-added tax, or an expenditure tax. Excise taxes can be collected at various stages, including the point of production, the wholesale level, or the retail level. They are also known as selective sales taxes or differential commodity taxes.

Excise taxes are levied on either a unit or ad valorem basis. For unit (also known as specific) excises, the tax is denominated in terms of money per physical unit produced or sold. Examples include the federal government taxes of 18.4 cents per gallon of gasoline, $13.50 per gallon of distilled spirits, and $3.10 per domestic flight segment for passenger airline travel. Ad valorem excises are based on a percentage of the value of the product or service sold. The 7.5 percent federal tax on the cost of domestic airline passenger tickets and the 3 percent tax on the cost of telephone services are examples of ad valorem taxes.

Broader-based taxes, such as the income and general sales taxes, are difficult to administer when most of the economic activity takes place outside a structured market setting. Excise taxes are sometimes used as a means of implementing an ability-to-pay approach to taxation. So-called luxury taxes are an example of this approach.1 The United States currently levies an excise tax on expensive passenger vehicles. This tax is set at 10 percent of the value in excess of a floor amount of $30,000. The tax on high-value automobiles has also been explained as a means of making foreign imports (which comprise a large percentage of such vehicles) more expensive than domestic Automobiles. By taxing items consumed disproportionately by higher-income individuals, excise taxes can achieve an element of progressivity. There are questions, however, concerning horizontal equity because not all people at the same income level have similar expenditure patterns for luxury items.  Excises are also levied on goods or services that are considered harmful or undesirable, in an Attempt to discourage consumption. Taxes based on this rationale are labeled sumptuary excises.  Examples include taxes on alcoholic beverages, tobacco products, and wagering. Because many of the goods and services taxed by sumptuary excises have relatively inelastic demands, these taxes May have only a limited impact on curtailing consumption. This presents an added benefit, however, for the government in that it provides a relatively stable source of tax revenue. Sumptuary Taxes are often popular politically because many citizens do not engage in the taxed activities, whereas purchasers of the taxed items do so voluntarily. Such taxes may have negative consequences from the standpoint of vertical equity because sumptuary excises are often highly regressive. Excises may also be imposed as a technique for dealing with negative externalities. This is related in some ways to the sumptuary excises. Taxes on “gas guzzling” automobiles and gasoline can be explained as a kind of Pigouvian (corrective) tax to reduce the divergence of the private and social costs relating to pollution or congestion. Such taxes are usually an imperfect technique for internalizing externalities, because an efficient Pigouvian tax should be related to the marginal damage caused by an activity, which is not necessarily proportional to the level of consumption.

Finally, excise taxes may be employed as a means of implementing a benefits-received approach to taxation. Gasoline taxes are an example. Gasoline usage is closely related to highway travel, thereby providing a link between taxes paid and benefits received from roadways. This link is further strengthened by earmarking where the revenues collected from an excise tax are designated for use in providing government services related to the activity. Examples include the earmarking of motor fuel taxes for highways and taxes on airline tickets for air traffic control and facilities expansion.  

Continue reading
  19688 Hits

የግል አቤቱታ የማቅረብ መብት በጠቅላላው

 

መግቢያ

የሥነ-ሥርዓት ሕግ ሰዎች መሠረታዊ የሆኑ የፍትሕ አቤቱታዎች ሲቀርቡ የሚመሩበትን እና መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት የሚወስኑበትንና ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚያሳይ ጽንሰ ሀሳብ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕግ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በምንና እንዴት ባለ አኳኋን ወደ ተግባር ሊፈፀሙ እንደሚችሉ የሚዘረዝር የሕግ ክፍል ነው። የእነዚህን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች ይዘትና አይነት ተንትኖ የሚያቀረበው የሕግ ክፍል መሠረታዊ ሕግ (Substantive Law) ተብሎ የሚጠራ ነው። መሠረታዊ ሕግ የሰው ልጆችን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በግልፅ የሚደነግግ በመሆኑ ጠቀሚታው ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል። ይሁን እንጅ እንዚህ ዝርዝር መብቶችና ግዴታዎች በተግባር ተፈፃሚ እንዲሆኑ ካልተደረገ የመኖራቸው ጉዳይ ትርጉም የለሽ ይሆናል ማለት ነው። እነዚህ መደበኛና ልዩ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች እንዲፈፀሙ የማድረጉ ሐላፊነት የሥነ-ሥርዓት ሕግ ቢሆንም ውጤታማ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከሌለ ግን መብቶችንና ግዴታዎችን የማስፈፀሙ ዓላማ እረብ የለሽ ይሆናል። ለዚህም ነው የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከመሠረታዊው ሕግ ባላነሰ አስፈላጊና ጠቃሚ ነው የሚባለው።

በግልፅ መረዳት እንደሚቻለው ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ያለው አስተዋፆ በጣም ከፍተኛ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕጉን ዓላማና መንፈስ መከተል ተከትሎም ተፈፃሚ ማድረግ በራሱ ፍትሕን ማረጋገጥ ነው የሚሆነው። የፍትሕ ጉዳይ ‹‹የትም ፍጪው ዱቂቱን አምጭው›› የምንለው ነገር ሣይሆን ከመነሻው እስከ መዳረሻው ያለውን ሂደትና ሥርዓት በመከተልና በመተግበር የሚገኝ ፍርድ ስለሆነ የሥነ-ሥርዓት ሕጎችን እውቀት ማሳደግ ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ ቁልፍ ሚና አለው።

የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥዓት የወንጀል ጉዳዩች የሚመሩበት የሚከሰሱበት የሚዳኙበት የሚቀጡበትን  ሥርዓቶች  የሚገዙ ደንቦች  ናቸው።  ይህም  ትንሽ  የማይባሉትን የመሠረታዊ ወይም የዋና መብቶች ደረጃ አግኝተው በሕገ-መንግስት እና  በዓለም-አቀፍ  ኮቬናንቶች ጥበቃና  አውቅና  ያገኙትን የተከሣሾች የሥነ-ሥርዓት መብቶች ያካትታል። 

Continue reading
  17600 Hits

Letters of Credit in General

 

Introduction

Letter of credit transactions have been developed since the middle Ages in connection with the trade of goods at the international level. Individuals and companies have found themselves dealing with partners of whom they know little, who are located in distant countries with often insecure political and economic situations. Furthermore, the dynamism of the actual economy creates a need for financing that requires a guarantee of payment at a time and for an amount that must be certain. Diversity in geographical nature, weather, climate, production system and globalization in culture and fashion has made the countries dependent on each other for the daily necessities. Similarly, one continent is, largely, dependent on the products of other continents. In addition, diversity in human appetite and attitude, unequal development of technology, desire for luxury, and the development of communication system and tale-communication, revolutionarily, increase the necessity of transnational, transcontinental business activities.

As far as the payment issue is concerned, market reality, distance, geographical barriers, uncertainty and lack of confidence among the business actors discourage the global commercial venture. In market reality, the buyer, always, wants to pay the seller only after selling the imported products in the internal market. On the other hand, the seller wants payment as soon as possible ‘if possible, even before shipment’. Moreover, in transnational business transaction, where the goods and the payment are not exchanged simultaneously there is a risk that parties to an exchange may not fulfill their obligations. In such a case the seller may take the payment and not give the good or the buyer take the good and not give the payment. Furthermore, trade transactions between different countries involve different payment systems, conflict of laws, barrier of languages, lack of understanding and reliability among the business partners and other barriers.

Fortunately, letter of credit (LC) or ‘documentary credit’ or ‘banker’s commercial credit’ has Brought a revolutionary solution to all this problems and has ensured sufficient securities and certainty in payment transaction.

Continue reading
  18902 Hits

ስለቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) ፍርድ ቤት ተልዕኮ፣ ሥልጣን እና ተግባር

 

መግቢያ

በዘመናዊ አሠራር የወንጀል ጉዳይን እንዲከታተል የተቋቋመ እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለፍርድ ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዩች አይነትና ብዛት ለመለየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ይቀይስለታል፡፡ ይህ እንዲሆን የሚያሰፈለገውም በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በሚከሰሰበትና ለፍርድ በሚቀርብበት ጊዜ ብዙ ችግር ሊገጥመው እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ በወንጀል ተግባር ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ ሰው የሚደርስበት የማሕበራዊና የኢኮኖሚያዊ ቀውስ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ አይነቱ ከባድ ጉዳት ሊደርስ የሚገባው በእርግጥ ወንጀል በሰሩና ወንጀል ለመስራታቸውም የማያጠራጠር ማስረጃ በቀረበባቸው ሰዎች ላይ መሆን አለበት፡፡ አንድን ሰው ወንጀል ሰርተሃል ብሎ መክሰስና በማሕበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለውን ክብር ዝቅ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ክሱን በማስረጃ ማረጋገጥና ተከሣሹን ጥፋተኛ ማስደረግ ግን በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ በማስረጃ ሊረጋገጡ የማይችሉ ወንጀሎች በተቻለ መጠን በአጭሩ መቋጫ እንዲያገኙ ማድረግ የመንግሥት ሃላፊነት ነው፡፡

ሁለተኛ የወንጀልን ጉዳይ በፍጥነት ውሣኔ ማሰጠት ሲገባ በልማድ እንደሚታየው ግን ይህን ማድረግ እንዲህ ቀላል ሆኖ አልተገኘም፡፡ በማንኛውም አገር እንደሚታየው የወንጀል ሥራ በየአቅጣጫው እየጨመረ በመሄድ ላይ የሚገኝ ቢሆንም እንኳን ሁሉንም ወንጀል አድራጌዎች ወዲያውኑ ወደ ፍርድ ቤት ለማቅረብና ለማስቀጣት አይቻልም፡፡ ከወንጀሎቹ ብዛት አንፃር ሲታይ ደካማወቹ ጉዳዩች በአጭሩ የሚቋጩበት ዘዴ መኖር አለበት፡፡ ከማስረጃ አኳያ ጠንካራዎቹን እና ደካማዎቹን ጉዳዩች የምናጣራበት ዘዴ ቀዳሚ ምርመራ በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ጠንካራዎቹን እና ደካማዎቹን ጉዳዩች የማበጠሩና የመለየቱ ተግባር እንደየ አገሩ የሕግ ሥርዓት ለዐቃቤ ሕግ ወይም ለመርማሪ ዳኛ (investigating Judge) ወይም የሕግ ሙያ ለሌላቸው እማኝ ዳኞች (Grand juries) ሊሰጥ ይችላል፡፡ ከፖሊስ የምርመራ መዝገብ የደረሰው ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩ በቀዳሚ ምርመራ አድረጌ ፍርድ ቤት መጣራት የሚገባው ሆኖ ካገኘው ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን እንዲያጣራ ሊያዝ ይችላል፡፡ ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩ ለቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ የሚሰጠው ምን ምን ሁኔታዎች ተሟልተው ሲገኙ ነው? ጉዳዩ ለቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት ሣያቀርብ በቀጥታ ክሱን በዳኝነት ለማየት ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ቢያቀርብ ሊመጣ የሚችለው ውጤት ምንድን ነውየቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍርድ ቤት ሥልጣን ተግባርና ዓላማ ምንድን ነው?

ከላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሽ ለማገኘት ቀዳሚ ምርመራን (ቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) በሌሎች ሐገራት Preliminary Hearing, Preliminary Examination ወይም Examining Trial በመባል ይጠራል) አስመልክቶ በሌሎች ሐገራት ያለውን የሕግ ማዕቀፍ ይዘትና አሠራር በቅድሚያ መመልከት አስፈላጊ ነው፡፡

Continue reading
  13589 Hits

ሕገ መንግሥታዊ የዋስትና መብትን በመተርጎም በኩል ስለታየው ችግር

 

መግቢያ

ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን ስምምነት& ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሕግጋት እና በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የተካተቱት ሥነ ሥርዓታዊ መብቶች መሠረታዊ ዓላማ መርማሪ አካላት ያለበቂ ምክንያትና ሕጋዊ ሥርዓት የአንድን ሰው የነጻነት መብት እንዳይጥሱ ዋስትና እና ጥበቃ መስጠት ነው፡፡ የብዙ አገሮች ሕገ መንግሥት የአንድ ሰው በሕይወት የመኖር& የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት ከሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክቡርነት የመነጩ ሊደፈሩና ሊገሰሱ የማይችሉ መብቶች መሆናቸውን ያረጋገጣሉ@ መሠረታዊ መብቶቹ ተግባር ላይ እንዲውሉ ጥረት የሚደረግ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ በሌላ በኩል የእነዚህን መብቶች አፈፃፀም የሚሸረሽሩ ወይም ዋጋ የሚያሳጡ የተለያዩ የወንጀል ድርጌቶች በዓለም ውስጥ በየደረጃው በስፋት ሲፈፀም ማየትና መስማት የተለመደ ሆኗል፡፡ ይህ የማይጣጣም ሁኔታ ከልዩ ልዩ የጥቅም ግጭቶች& ከአመለካከት ልዩነት& ካለመቻቻልና ከመሣሰሉት መንስዔዎች የሚመነጭ ሊሆን ይችላል፡፡

በዓለም አቀፍ ሆነ በብሔራዊ ሕግጋት ዕውቅና ከተሰጣቸው መሠረታዊ መብቶች አንዱ በወንጀል የተከሰሰ ሰው ጉዳዩ ሥልጣን ባለው ፍርድ ቤት ታይቶ ጥፋተኛ መሆኑ እስካልተረጋገጠ ድረስ ከወንጀል ነፃ እንደሆነ የመቆጠር መብት ያለው መሆኑ ነው፡፡ ይህ መሠረታዊ መብት ዕውቅና ሊያገኝ የቻለው ንፁሀን ግለሰቦች በወንጀል በመጠርጠራቸው ወይም በመከሰሳቸው ብቻ ሊደርስባቸው የሚችለውን የተለያየ የመብት ጥሰት ለመግታት ነው፡፡

ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ የተያዘ ሰው በመሠረቱ የተጠረጠረበት ወንጀል በማስረጃ ከተረጋገጠበት ሊፈረድበት@ ማስረጃ ከሌለ ግን ሊፈታ ይገባል፡፡ ሆኖም መረማሪ ፖሊስ ወይም ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩን እስኪያጣሩና ለፍርድ እስኪቀርብ ድረስ ታሣሪው በጥፋተኝነት የማይቀጣበት ወይም በፍጹም ነፃነት የማይለቀቅበት ሁኔታ አለ፡፡ ይህም በዋስ የመለቀቅ መብት ነው፡፡ መንግሥት የሕብረተሰብን ሰላምና ፀጥታ የማስከበር እንዲሁም የግለሰብን መብትና ነፃነት የማክበር ሃላፊነት አለበት፡፡ መንግሥት የወንጀል ተግባር ፈጽመዋል በማለት በሚይዛቸው ሰዎች ላይ ሕግ ለማስከበር የሚፈጽመው ተግባር ሁለት ተፋላሚ የሆኑ ጥቅሞችን የሚያስታርቅና የሚያቻችል መሆን አለበት፡፡ የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ሲባል በከባድ የወንጀል ተግባር የተጠረጠሩ ሰዎችን በፍርድ አደባባይ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ለማድረግ  ከፍርድ በፊት ማሰሩ ተገቢ ሲሆን በሌላ በኩል ተጠርጠረው የታሰሩ ሰዎች ንፁህ ሰዎች የሚሆኑበት እድል ሰፊ ስለሆነ ከፍርድ በፊት እንዳይታሰሩ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡  

Continue reading
  15229 Hits