Mr. Mulugeta Belay is a consultant and attorney at law. He is best known for his role as a 'Judge' on Chilot television drama

የሕግ የበላይነትን የሚያናጋው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ (የቤት ኪራይ ማእቀብና የሕግ ጥሰቶቹ)

 

መግቢያ

የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ቀደም ሲል አውጥቶት የነበረውና የተከራየን ሰው ማስወጣት (በርግጥ ደንቡ ይህን ድርጊት አልከለከለም) እና የኪራይ ዋጋን መጨመር ለማገድ የወጣውን የደንብ ቁጥር 122/13 ማራዘሙን በድጋሜ አስታዉቋል፡፡ ይህ ደንብ የቤት አከራዮች ያከራዬት ቤት ላይ ዋጋ እንዳንይጨምሩ ክልከላ ይጥላል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የደንቡን ህጋዊነት ለሕግ የበላይነት ያለውን መጥፎ ተምስሌትነት በርግጥ ሊፈታ ያሰበውን ችግር ለመፍታት ያለውን ፋይዳ በአጭር ባጭሩ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡ አንባቢያንን ለተራዘመ እና አሰልቺ የንባብ ሂደቶች ላለመዳረግ ጉዳዩን በቀጥታና በጭሩ ለመዳሰስም ተሞክሯል፡፡

Continue reading
  8069 Hits

ስለቅድመ ሳንሱር

 

ቅድመ ሳንሱር በማንኛውም ቅርፅ በማንኛውም አካል ክልል ነው።

ሰሞኑን ዎልታ ቴሌቪዥን ለማሰራጨት ያዘጋጃቸውን ፕሮግራሞች እንዳያሰራጭ የፍርድ ቤት ትእዛዝ እንደተሰጠ አድምጠናል።

የመናገር ነፃነትና የሚዲያ ነፃነት የሕግ እና የአሰራር ገደቦች የትላንት ከትላንት ወዲያ የጭቆና አርእስቶች ነበሩ።

ምንም አስብ፣ ምንም አቅድ መናገርና ሀሳብህን በስእል፣ በፅሁፍ፣ በሙዚቃ እና በየትኛውም ራስን የመግለፅ ጥበብ መግለጽ ተፈጥሮአዊ እና ህገመንግስታዊ መብት ነው።

Continue reading
  5643 Hits
Tags:

የዜግነት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ የቅድመ ሁኔታዎቹ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ:- ለአቶ ግዛው ለገሰ የተሰጠ ምላሽ

 

 

ስለ ዜግነት አዎጁ በፃፍኩት ጽሑፍ ላይ አቶ ግዛዉ ለገሰ የተባሉ የሕግ ባለሙያ የፃፉት ምላሽ ደርሶኝ ተመለከትኩት፡፡ (የአቶ ግዛው ለገሰ ጽሑፍን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ፡፡ ) በመጀመሪያ ጸሐፊው የሕግ ባለሙያ እንደመሆናቸውም ብሎም ጽሑፉን ያወጡት እሳቸው ስላልተስማሙበት የሕግ ጽሑፍ ምላሽ ለመስጠት እንደ መሆኑ አቶ ጀዋር መሐመድን ለመደገፍ አልፃፍኩትም ለማለት አቶ ጀዋር የራሱ ጉዳይ ብለው ጽሑፉን መጀመራቸው፤ በጽሑፉ ውስጥ ለተነሱ እያንዳንዱ ክርክሮች ተገቢውን የሕግ ክርክር ከማንሳት ይልቅ በአመዛኙ በተራ የአዋቃለሁ ባይነት ጉራ ተሞልተው እኩይ ሴራ የሚሉ ያልተገቡ ቃላቶች መጠቀማቸው ብሎም በጽሑፉ ውስጥ  ለድምዳሜቸው ማስረጃ አድርገው ስላቀረቡት የሕግ ግምት (presumption of law) ምንነት ያሉት ነገር አለመኖሩ እና ሃሳባቸው ልክ ስለመሆኑ የሚደግፍ የሕግ አስተምሮ ሳይጠቅሱ በደፈናው የሕግ ግምት ያልገባው የሚል የወረደ ምላሽ መስጠታቸው ከሙያ ሥነ-ምግባር የወጣ ተራ ብሽሽቅ የመሰለ መውረድ ሆኖ አግንቼዋለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ የመጀመሪየው ጽሑፍ በግልፅ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት ላይ ብቻ አተኮሮ እንደተፃፈ በተገለፀበት ሁኔታ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ስለሌላቸው እንደ በሕግ ዜግነት ስለማግኘት የመሳሰሉ ለምላሹ ፋይዳ በሌላቸው ዝርዝሮች ላይ ማተኮራቸውም አስቀድመው ላልተስማሙበት ጽሑፍ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በቂ እድል ነፍጓቸዋል ጊዜያቸው አጥንቱን በመጋጥ ላይ መዋል ሲገባው መረቅ ለመጠጣት ውሏል፡፡

እንግዲህ ከዚህ ቀጥየ የአቶ ግዛው የክርክር ነጥቦችን በእኔ መረዳት በሕግ እና በክርክር መርሆች አይን ስሁት መሆናቸውን እንደሚከተለው አሰረዳለሁ፡፡ ትክክለኛው እና አሳማኙ ክርክር የማን ነው የሚለው መዳረሻ የአንባቢ እንጂ የጸሐፊዎች ባለመሆኑ እንደ አቶ ግዛው የኔ ሃሳብ የጉዳዩ ዳርቻ ነው የሚል ትዕቢት አይዳዳኝም፡፡ በጉዳዩ ላይ ስፅፍም የጉዳዩ ትኩረት ማግኘት ትኩረት ከመሳቡ ውጭ የተለየ አትኩሮት ለጉዳዩ እንደሌለኝ በቅንነት ስገልፅ ይህን ማመን ወይም መጠራጠር በእጃችሁ ነው፡፡

የአቶ ግዛው ጽሑፍ አልፋ እና ኦሜጋ በዜግነት አዋጁ ላይ የተጠቀሱት ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች የሕግ ግምት በመሆናቸው ያለምንም የተለየ ሥርዓት ዜግነት ያሰጣሉ ቅድመ ሁኔታዎቹ አልተሟሉም ካለ ማስረጃ የማቅረብ ሃላፊነት (የማስረዳት ሸክም) የኮሚቴው ነው የሚል ነው፡፡

Continue reading
  7419 Hits
Tags:

የኢትዮጵያ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት - የኢትዮጵያ ዜግነትን ያለባለሥልጣኑ (ኤጀንሲው) ውሳኔ መልሶ ማግኘት የማይቻል ስለመሆኑ

 

ሰሞኑን የአቶ ጀዋር መሐመድን ኢትዮጵያዊ ዜግነት መልሶ የማግኘት ጉዳይ በኦፌኮ እና በምርጫ ቦርድ መካከል ክርክሮችን ማስነሳቱን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየሰማን እንገኛለን፡፡ በመሆኑም የዜግነት ሕጉ ኢትዮጵያዊ ዜግነት መልሶ ስለማግኘት ስላሰቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች እና ዜግነት መልሶ ማግኘት ስለሚረጋገጥበት መንገድ ያለኝን መረዳት ለማካፈል ወደድኩኝ፡፡

አቶ ጀዋር መሐመድ አስቀድመው የኢትዮጵያ ዜጋ የነበሩ በመሆናቸው ነገር ግን በሕግ ዜግነታቸውን ከቀየሩ በኋላ መልሰው ዜግነታቸው እየጠየቁ በመሆኑ ለዚህ ጉዳይ ተገቢነት ያለው ድንጋጌ ስለዜግነት የሚደነግገው የአዋጅ ቁጥር 378/96  አንቀፅ 22  እና 23/2/ሐ ነው፡፡ በዚህ መሠረትም ኢትዮጵያዊ የነበረ ነገር ግን በሕግ የሌላ ሀገር ዜግነት ያገኘ ሰው የሚከተሉትን መሠረታዊ ጉዳዮች ከተሟሉ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን መልሶ ያገኛል፤

  1. አስቀድሞ ኢትዮጵያዊ የነበረ መሆኑ፤
  2. ወደኢትዮጵያ ተመልሶ በመምጣት መደበኛ መኖሪያውን በኢትዮጵያ ውስጥ ከመሠረተ፤
  3. ይዞት የነበረውን የሌላ ሀገር ዜግነት ከተወ፤
  4. ዜግነቱ እንዲመለስለት ለኢሚግሬሽን እና ስደተኞች ባለሥልጣን ካመለከተ፤
  5. ጥያቄው ለዜግነት ጉዳይ ኮሚቴ ቀርቦ በባለስልጣኑ ተቀባይነት ካገኘ፡፡

ከፍ ሲል በዝርዝር የተመለከቱ ጉዳዮች አንድ ሰው ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን መልሶ ለማግኘት ቅድመ ሁኔታዎች በመሆናቸው እና እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች የተሟሉ መሆን አለመሆናቸውን የማረጋገጥ እና የውሳኔ ሐሳብ የመሰጠት ሥልጣን ደግሞ የዜግነት ጉዳይ ኮሚቴ በመሆኑ በአዋጁ አንቀጽ 23/3 መሠረት የዜግነት ይመለስልኝ ጥያቄው በባለሥልጣኑ አማካኝነት ለኮሚቴው ቀርቦ ኮሚቴው የውሳኔ ሃሳብ ለባለሥልጣኑ አቅርቦ መወሰን ይገባዋል፡፡

Continue reading
  10284 Hits
Tags:

የማናከብረውን እና የማንተገብረውን ሕግ ማውጣት ከሕግ አልባነት አይሻልም- መረጃ የማግኘት መብት

 

ሕግ ጭራሽ ካለመከበሩ በከፋ ተመርጦ ሲከበር የበለጠ አልተከበረም፡፡ አሁን ባለን መረጃ ሀገሪቱ ከቻይና ጋር ስለገባነው የብድር ስምምነት የሚያትትውን 1000ኛውን አዋጅ ካወጀች ብኋላ  እንኳ ከመቶ በላይ አዋጆች ወጥተዋል፡፡ ኑሮው፣ ፖለቲካው፣ ኢኮኖሚውና ማህበራዊ ጉዳያችን ብዙ ነው እና ሕጎቹ በዙ አይደለም ጉዳዩ፡፡ ስንቱ በርግጥ ወጥቶ ሥራ ላይ ዋለ ነው ጥያቄው፡፡ የማናከብረውን እና የማንተገብረውን ሕግ ማውጣት ከሕግ አልባነት አይሻልም፡፡ 

ይህ ጽሑፍ ስለ መረጃ ነፃነት ነው፡፡ ሰብአዊና አለማቀፋዊ የሆነው የመረጃ ነፃነት  መብት ተጥሷል፡፡ በአጭር ቋንቋ ህገ መንግስቱ ተጥሷል፡፡ የተጣሰው ደግሞ ህጉ በወጣለት ህዝብም ፤ ህጉ በወጣበት መንግስትም ፤  ህጉ በወጣላቸው ሚዲያዎችም ጭምር ነው፡፡

ሁሉን ብፅፍ ቀለም አይበቃም እንዲል ሊቁ እኔ ግን እናተን በረጅም ጽሑፍ ላለማሰልቸት  እንደሚከተለው አሳጥሬዋለሁ፡፡ በሕገ መንግሥቱ የተከበረው እና የታፈረው የዜጎች መረጃ የማግኘት መብት በሚዲያዎች እና በመንግስት ተቋማት በአደባባይ እየተሻረ ነው፡፡ ግልፅ ነው ዜጎች ስለማናቸውም ጉዳይ እጅግ ውስን ከሆኑ በስተቀሮች በቀር መረጃ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ዴሞክራሲ ጎዞ ጀምሯል የሚባለው ጠያቂ ሚዲያ ፣ መለሽ መንግስትና አድማጭ ህዝብ ሲኖርም ጭምር ነው፡፡ ያለ መረጃ ነፃነት ዴሞክራሲ የለም አይኖርምም፡፡ ካልተማሩ እንዴት ያውቃሉ ካላወቁ እንዴት ይጠይቃሉ እንዲል መጽሐፍ የመረጃ ነፃነት ወይም መረጃ የማግኘት መብት የዴሞክራሲ አምድ ነው፡፡

ሚዲያዎች መንግስት ሃላፊዎችን እና የመንግስት ተቋማትን የሚያጋልጡ መረጃዎችን ጨምሮ ማናቸውንም የህዝብ መረጃ የመጠየቅ ጠይቆ የማግኘት መብትም ግዴታም አለባቸው፡፡ መንግስት እጅግ ጥቂት ከሆኑ እንደ ሃገር ደህንነት የሚመለከቱ ጉዳዮች በቀር ምን? ለምን? እንደሚሰራ ዜጎች የማወቅ እና በጉዳዩ ላይ በሻቸው መንገድ ሃሳባቸውን የመግለፅ መብትና አቋም የመያዝ መብት አላቸው፡፡ ጉዳዩ አዋጃዊ አይደለም ህገመንግስታዊ ጭምር ነው፡፡  ስለዚህ  ይህን መብት አለማክበር ህገ- መንግስትን አለማክበር ነው፡፡ ህገ-መግስት አልተከበረም የሚባለው የየግል ቁስላችን ሲናካና ትላንት ድንጋይ ወደ መንግስት ሲወረወር  ዛሬ የፌደራል ስረአቱ ሲነካ ብቻ አይደለም ፡፡ በህገ-መግስቱ በግልፅ እና በቅድሚያ የተደነገጉት የግለሰብ እና የህዝብ መብቶች ሲጣሱም ጭምር ነው፡፡ የህገ-መንግስቱን  መጣስ ሁሌ ከፌደራል ስረአት መከበር አለመከብር ጋር ማያያዝ ህገመግስቱ  ለግለሰቦች የሰጣቸውን በረጅም የህዝቦች ትግልና መሰዋትነት  አለማቀፋዊነት ደረጃ ያገኙ  መብቶችን መጣስ ነው፡፡ መቼስ ስረአቱ የተዘረጋው ለህዝቦች መብት ሰላም እና ደህንነት ከሆነ የግለሶችን እና የህዝቦች መብት እየጣሱ ስረአቱን መጠበቅ ውሃውን እያፈሰሱ  ቧንቧውን እንደመንከባከብ ያለ አባካኝነት ነው፡፡

Continue reading
  7994 Hits

በፍርድ ከሄደች በቅሎየ ያለፍርድ የሄደች ጭብጦየ (ለውጥ የሚሹ የፍርድ ቤት ጉዳዮች)


ፍርድ ቤት የበደል ስር የሚቆረጥበት ፤ ተበዳይ የሚካስበት፤ አጥፊ የሚቀጣበትና መንግስት ከህግ በታች መሆኑ የሚረጋገጥበት መድረክ ነው፡፡ ፍርድ ቤት ፍትህ ከረቂቅነት ከፍ ብላ የምትታይ ፣ የምትሰማ እና የምትዳሰስ ህልው መሆኗ የሚታወቅበት አደባባይ ነው፡፡ ፍርድ ቤት የሰለጠነ ህዝብ የኔ የሚለውን ህግ የሚያስከብርበት መሳሪያ ነው፡፡ ህይወቱ ፣ ንብረቱና የኔ የሚላቸው እሴቶቹ ሁሉ ጥበቃ ያላቸው ስለመሆኑ የሚተማመንበት ዋሱ ነው ፍርድ ቤት፡፡


የምትታሰረው ፣ የምትፈታው፣ ከአታላዮች ገንዘብህን የምታስመልስው፣ ስሜ አስጠላኝ ልቀይር ፣ ትዳር ከበደኝ ልፋታ ካልክ መሄጃህ ፍርድ ቤት ነው፡፡ ሞት የሚፈርደብህ፣ ቀሪ ዘመንህን በአንድ የተከለለ የቆርቆሮ ግቢ ውስጥ በጥበቃ ስር ሆነህ እንድታሳልፍ የምትገደደውም በፍርድ ቤት ነው፡፡ ተበድያለሁ ልካስ ፣ በድሏል ይቀጣ ፣ የመናገር ነፃነቴ ይከበር ፣ የመዘዋወር መብቴ ተገደበ ብለህ የምትጮህውም ፍርድ ቤት ነው፡፡ ክብሬ ተንክቷል ልከበር ፣ ስሜ ጠፍቷል ይታደስ ፣ ገንዘቤ ተወስዷል ይመለስ ማለት የምትችለውም በዚያው ነው፡፡ አርእስቱን የተቀኘው ባለቅኔም በፍርድ ከሄደች ብዙ ዋጋ ከምታወጣው በቅሎው ይልቅ ያለፍርድ የሄደችው በሳንቲም የምትተመነው ጭብጦው የቆጨችው ያለፍርድ በዘፈቀደ የሚደረግ ድርጊት የፍትህ መዛባት የፍርድ መጓደል አድርጎ ስለሚመለከተው ነው፡፡


ታዲያ ይህን ሁሉ ማድረግ የሚችሉት ፍርድ ቤቶቻችን እነዚህን ጉዳዮች በጊዜው ፣ በእኩል እና ያለአድሎ ለመፈጸም በሚያስችላቸው ቁመና ላይ ይገኛሉ? በርግጥስ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚታመን ሲቀጣም ሲፈታም ልክ ነው የሚባል ፍርድ ቤት ገንብተናል? ፍትህ ለሁሉም በግዜው ተደራሽ ሆኗል?


ፀሃፊው ለጥያቄዎቹ የሚሰጠው ምላሽ ከፁሁፉ አርእስት ጋር አንድ እና ያው ነው፡፡ ይህ ፅሁፉ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ክብርት ፕሬዝዳንቷ ከመሾማቸው ቀደም ብሎ ለንባብ ለማብቃት ታስቦ በመሃል ክብርት ፕሬዝዳንቷ በመመረጣቸው የፅሁፉ ፋይዳ ከትችት ወደ ቸግር ተቋሚነት ከፍ ብሏል፡፡ የትላንቱ የፍርድ ቤት ዘመን አጥፍቶም ሆነ አልምቶ አልፏል፡፡ ለለውጥ የተሾሙት እና የሚሾሙት አዲስ ሀይሎች የትላንቱን ችግር መፍትሄ ማፈላለጊያ በማድረግ አዲስ ዘመን እንደሚያነጉ ይታመናል፡፡
ይህ ፅሁፍ መንግስት ለፍርድ ቤቶች ትኩረት ከመንፈጉ የተነሳ፣ በተበላሸ አስተዳደር ምክንያት ፣ ለሙግት ምክንያት የሚሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ቤቶችን በማጨናነቃቸው ሳቢያ ፣ ለነሱም ትኩረት እና ምስጋና ሳይቸራቸው በሚቻላቸው መጠን በችግሮቹ መሀል ያላቸውን የሰጡ ለሀቅ እና ለፍትህ የቆሙ ዳኞችን አይመለከትም፡፡ ይልቁንስ በዚህ ችግር መሃል የቻሉትን አድርገዋል እና ምስጋናየ ይድረሰቻው፡፡ ይልቁንም ፅሁፉ ለችግሮቹ ዋና ምክንያት የሆኑትን የትኩረት ማጣት፣ የአስተዳደር ብልሽት እና ስሁት የሆኑ የፖሊሲ ጉዳዬች ላይ ያተኩራል፡፡


ዳኛ መሆን የሚገባው ማን ነው፡፡

Continue reading
  10516 Hits
Tags:

ደብዳቤው

ያው ጉባኤው የሚለውን ርእስ መኮረጄ ነው

እየመረጥክ ከዘገብክ የገለልተኝነት እና የእኩልነትን መርህ ጥሰሃል፡፡

/በበውቀቱ እስታይል/

ተከታዮ የመጀመሪያ አንቀፅ ለአገላለፅ ውበት እንጅ በጉዳዩ ላይ ያለኝ መቆጨት እንዳገላለፁ አለመሆኑ ይታወቅልኝ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሮድካስቲንግ ባለስልጣል ለኢ ኤን ኤን የቴሌቪዚን ጣቢያ የፃፈውን ደብዳቤ እዚህ የፌስቡክ መንደር ውስጥ እያወቁ በድፍረት ሳያውቁ በስህተት እንደሆን እንጃ እጅጉን ሲተች ባይ ሆድ ባሰኝ፤ እንባየ መጣ ፤ቁጭት ልቤን መዘመዘው፤ አላስችል አለኝ በመጀመሪያ መብት የለውም አሉ ዝም አልኩኝ እነሱ ግን ይህን ሳያርሙ ሌላ ገደፉ እንዴት  ማለት ሲገባቸው ስህተት ነው ብለው ተናገሩ፡፡ በዚህ መች አብቅተው  እኩልነት ተጥሷል እል ብለው የሀሳብ ነጻነት ተደፍሯል ብለው አረፉ እንግዲህ ይህን ዝም ብሎ ማለፍ እንደምን ይቻላል፡፡ ምእመናን  አሳምራችሁ እንደምታወቁት የመገናኛ ብዙሃን መሰረት ገለልተኝነት እና በእኩልነት መርህ መገዛት አይደለምን? የመረጃ ነጻነት አደጋ ላይ የወደቀው እነዚህን መርሆች በጥብቅ ባለመከበራቸው መሆኑስ ይዘናጋል ምእመናን፡፡ እነዚህን መርሆች አለማክበርስ የመገናኛ ብዙሃንን ሃላፊነት በቅጡ ካለመረዳት የመጣ አይደለምን? መቼም ይህን ለማወቅ በዘርፉ ሙህር መሆን ይጠይቃል እያልኩ አይደለም ጎበዝ አስተዋይ ለሆነ ሰው ባለፈው ግዜ ሚዲያዋች የሰሩትን በማየት  ሚዲያዎቹ አድር ባይ የመንግስት አፈ ቀላጤ የነበሩ መሆናቸውን  መረዳት ይቸግረዋል ወይ ምእመናን? ስለዚህ እንደኔ እንደኔ ይን ጉዳይ በቀላሉ ልናልፈው አይገባም ባይ ነኝ፡፡

Continue reading
  8090 Hits

የቴዲ አፍሮ አልበም ምርቃት ክልከላ እና የመሰብሰብ መብት

 

መንደርደሪያ

የዚህ ጽሑፍ መነሻ የቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ መከልከል ሲሆን ጽሑፉ ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት በማንኛውም ምክንያት መሰብሰብ አድማሱ እስከምን ነው? የሚለውን መሠረታዊ ነጥብ የሚዳስስ ሲሆን የአልበም ምርቃቱን መከልከል ምክንያቶች በተመለከተ ግን ጸሐፊው በሁለቱም ወገኖች በኩል ያለውን እውነት በማስረጃ ባለማረጋገጡ አቋም ከመያዝ ተቆጥቧል፡፡ ይሁን እንጂ አጋጣሚው በአስፈፃሚውም ይሁን በስብሰባ አዝጋጆቹ ብሎም በማህበረስቡ ላይ ያለውን መደናገር የመሰብሰብ መብትን አድማስ ለማብራራት ምቹ በመሆኑ ጸሐፊው በርግጥ ለቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ ፈቃድ ያስፈልግ ነበር? ፈቃድ ካስፈለገውስ መከልከል ይቻል ነበር? የመከልከል ተግባሩ የሚጥሳቸው መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችና መብቶችስ ምንምን ናቸው? ለሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ይሞክራል፡፡

መግቢያ

መሰብሰብ ሰው ሁለት ሆኖ ከተፈጠረበት የታሪክ አውድ ይጀምራል፡፡ ሰው ማህበራዊ እንስሳ ነው ሲባል በሌላ አነጋገር ሰው ይሰበሰባል እንደ ማለት ነው፡፡ ፈጣሪም አዳም ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ሲል ጥንትም ፈጣሪ ሰውን ሲፈጥረው በውስጡ ከሌሎች ጋር የመሆን፣ ከሌሎች ጋር የመምከር፣ ከሌሎች ጋር የመደሰት፣ የመኖር፣ አንድን ነገር በጋራ የማድረግ፣ የማክበር ባሕርይ እንደፈጠረበት ሲያጠይቅ ነው፡፡ እናም መሰብሰብ ከፍ ሲል ፈጣሪ ለአዳም/ለአደም ሄዋንን/ሃዋን ሲፈጥርለት ዝቅ ሲል አዳምና ሄይዋን ቃዬልን ጠርተው ስለ አቤል ጉዳይ ሲጠይቁት ይጀምራል፡፡

Continue reading
  12578 Hits

የዘገየ ፍርድ

                እኔ አንቺን ስጠብቅ

ጠበኩሽ እኔማ…….

እዚያው ሰፈር ቆሜ

በአክሱም ቁመና በላሊበላ ዕድሜ

እግሮቼን ተክዬ ቀኔን አስረዝሜ

Continue reading
  12645 Hits

DNA አባትነትን ማረጋገጫ ማስረጃ ስላለመሆኑ

 

ሁሉም ሰው ባዮሎጂካዊ አባት አለው ሁሉም ሰው ግን ህጋዊ አባት ላይኖረው ይችላል፡፡ ይህ አረፍተ ነገር በብዙዎቻችሁ ጭንቅላት እንዴ! የሚል ግርምት እንደሚያጭር እገምታለሁ፡፡ በተለይ ሁሉም ልጅ እኩል ነው ልጆች አባትና እናታቸውን የማወቅ ሕገ መንግሥታዊ መብት አላችሁ የሚለው አነጋገር አብዝቶ ከመሰማቱ የተነሳ በሕግ አባት የሌለው ልጅ ሊኖር ይችላል ብሎ መገመት ሩቅ ሊሆን ይችላል በቀጣዩ ጽሑፍ በመግቢዬ የገለፅኩት ሀሳብ ምን ያህል እውነት እንደሆነ ለማሳየት እታትራለሁ፡፡

በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 36(1)(ሐ) ላይ ለህፃናት ከተደነገጉላቸው መሠረታዊ መብቶች አንዱ ህፃናት እናት አባታቸውን የማወቅ የእነሱንም ክትትልና እንክብካቤ ማግኘት ነው፡፡ ታዲያ ይህ ጥያቄ ተግባራዊ ምላሽ ሊያገኝ የሚችለው በየክልሎቹ የቤተሰብ ሕግና በፌደራሉ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ መሠረት ነው፡፡ ይሁን እንጂ በነዚህ የቤተሰብ ሕጎች ላይ ሁሉም ልጆች እናታቸውን እንጂ አባታቸውን ለማወቅ አልታደሉም የዚህ ጽሑፍ ማጠንጠኛም እነዚህ በሕግ አባታቸውን ለማወቅ ማወቅ አይደለም በሕግ አባት የሌላቸው ልጆች በእንዴት አይነት ሁኔታ የተወለዱ ልጆች ናቸው እጣፋንታቸውስ ምንድን ነው የሚለውን ሀሳብ መፈተሸ ነው፡፡ በተለይም ከእውነትነቱ ይልቅ በእምነትነቱ ይበልጥ የሚገለፀው የአባትንት ጥያቄ በቤተሰብ ሕጉ እንዴት ይመለሳል በተለይም ይህን ጥያቄ ከመመለስ ብኋላ የሚከተሉትን ሌሎች ይሕግ ጥያቄዎችን (ውርስ፣ቀለብ…) ባግባቡ ለበመልስ ይዚህ ጥያቄ ምላሽ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡

በሕግ የአንድ ልጅ አባት ማነው?

እንግዲህ የአንድን ልጅ አባትና እናት ለማወቅ በመጀመሪያ መመልከት ያለብን በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ስለ እናትነትና አባትነት ስለማወቅ የተደነገገበትን የሕግ ክፍል በመመልከት ነው በዚህ የሕግ ክፍል መሠረት የአንድን ልጅ አባት በሶስት የተለያዩ መንገዶች ማወቅ ይቻላል፡፡

Continue reading
  25023 Hits
Tags: