ጸሐፊው በባሕርዳር ዩኒቨርስቲ የሕግ መምህር ሲሆን በሕግ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ድግሪ አላቸው። ጸሐፊው በኢሜል አድራሻችው muhmetgusl@gmail.com ማግኘት ይችላሉ። 

በኢትዮጵያ ከሕግ አገልግሎት የሚሰበሰብ የተጨማሪ እሴት ታክስና የተርን ኦቨር ታክስ አዙሪት ጥያቄዎችና መውሰብስቦች

በኢትዮጵያ የታክስ አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የተርን ኦቨር ታክስን በመጠቀም ከሕግ አገልግሎት ሽያጭ ላይ ታክስ እንደሁኔታው በፌዴራሉ እና በክልል መንግሥታት በመጣሉ በተግባርም እየተሰበሰበ ይገኛል። ይሁን እንጅ ይህ ታክስ ሕጋዊ መሠረቱን እና አግባብነቱን በተመለከተ፤ ከታክስ መሠረቱ፣ ከታክስ ምጣኔው እና ከአስተዳደር ሂደቱ ጋር ተያይዞ በርካታ አዙሪት ጥያቄዎችና መውሰብስቦች ይስተዋላሉ፡፡ የዚህ ጥናት ዓላማም አነዚህን አዙሪት ጥየቄዎችና መውሰብስቦች በዓይነታዊ የምርምር ዘዴ በማጥናት የመፍትሔ ኃሳብ መጠቆም ነው፡፡ ለዚህም ያስችል ዘንድ የተለያዩ መዛግብቶች፣ ቃለመጠይቆችና ቡድንተኮር ውይይቶች በግብዓትነት ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን  ለንፅፅር ይረዳ ዘንድ የሌሎች አገራት ተሞክሮንም ለመቃኘት ተሞከሯል፡፡ በዚህም መሠረት ጥናቱ ባለሶስት አማራጭ የመፍትሔ ኃሳብ ያቀረበ ሲሆን የመጀመሪያው አሁን ከሕግ አገልግሎት በአገሪቱ እየተሰበሰበ ያለውን የሽያጭ ታክስ እንዳለ በማስቀጠል ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሕገመንግስታዊ መብቶች መከበር ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር መወሰድ ያለባቸውን ርምጃዎች አመላክቷል፡፡

  2330 Hits