Latest Blog posts
Editors Pick
Latest documents
Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023 7120 Downloads - policies and strategies | 7.6 MB | |
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy 163 Downloads - Arbitration Law | 635.59 KB | |
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25 8047 Downloads - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions | 10.72 MB | |
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED 350 Downloads - Criminal Law | 317.19 KB | |
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25 9940 Downloads - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions | 6.57 MB |
Legal News - የሕግ ዜናዎች

Abyssinia Law is the Ethiopian's leading legal news and information network for lawyers and other legal professionals. Read up-to-date legal news including civil trials, guilty verdicts and plea deals.
- Details
- Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች
ፖሊስ ሌሎች ያልተያዙ አሉ ብሏል
ተጠርጥረው በተያዙት ሦስት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ላይ የፌዴራሉ ፍርድ ቤት ለሁለተኛ ጊዜ ተጨማሪ የአሥር ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ፡፡
ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ካዋለችው የ‹‹ዞን ናይን›› ጦማሪያንና ጋዜጠኞች መካከል ስድስቱን በሁለት መዝገብ ከፍሎ ዛሬ ሚያዚያ 29 ቀን 2006 ዓ.ም. ለፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት አቅርቧል፡፡
በመጀመሪያው መዝገብ የቀረቡት የዞን ናይን አባላት የሆኑት ናትናኤል ፈለቀ፣ አጥናፍ ብርሃነና ኤዶም ካሣዬ ናቸው፡፡ በሁለተኛው መዝገብ የቀረቡት ደግሞ ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና ጦማሪ ዘለዓለም ክብረት ናቸው፡፡ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን የተመለከተው በዝግ ቢሆንም ከተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ለመረዳት እንደተቻለው፣ ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ በሽብርተኝነት ከተፈረጀ ድርጅት ጋር በመገናኘት፣ ሥልጠና በመውሰድና ገንዘብ በመቀበል አገርና ሕዝብን ለማሸበር ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ፖሊስ ገልጿል፡፡ በተቀበሉት ገንዘብም ላፕቶፕና ሌሎች የጽሕፈት መሣሪያዎችን ገዝተዋል ብሏል፡፡
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሌሎች ያልተያዙ በመኖራቸው፣ ያልተተረጐሙ መረጃዎች እስኪተረጐሙና በሌሎች ምክንያቶች ተጨማሪ የ15 ቀናት ጊዜ ፖሊስ መጠየቁንና ፍርድ ቤቱ የአሥር ቀናት ተጨማሪ ጊዜ በሁለቱም መዝገቦች መፍቀዱን ከጠበቆች ለመረዳት ተችሏል፡፡
- EthiopianReporter By
- Hits: 34763