Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

አቶ ኤርሚያስ አመልጋ የ500 ሺህ ብር ዋስትና ተፈቀደላቸው

የቀድሞው የአክሰስ ሪል ስቴት ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ አመልጋ የ500 ሺህ ብር ዋስትና ተፈቀደላቸው።

መርማሪ ፖሊስ ከተጠርጣሪና ከምስክሮች ቃል መቀበልን ጨምሮ የሰነድ ማስረጃዎችን መሰብሰብ፣ በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ማስረጃዎችን እንዲልኩ ማድረግ የሚሉትና መሰል ስራዎችን ሰርቺያለሁ በማለት ለቀሪ ስራዎች የ14 ቀን ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።

የአቶ ኤርሚያስ አመልጋ ጠበቆችም ፖሊስ የተሰጠው ጊዜ በቂ በመሆኑ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ሊሰጠው አይገባም ሲል ሞግቷል።

ይህ ቢሆን እንኳን የዋስትና መብት ይጠበቅልን ሲሉ አመልክተዋል።

መርማሪ ፖሊስ ግን አቶ አቶ ኤርሚያስ የተጠረጠሩበት ወንጀል ውስብስብና ሌሎች ተጠርጣሪዎችም በመኖራቸው ዋስትና ሊሰጥ አይገባም ብሏል።

የግራ ቀኙን ክርክር ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ባለፈው የመጨረሻ የሚል ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መስጠቱን ተከትሎም መርማሪ ፖሊስ የተሰጠው ጊዜ በቂ ነው በማለት ለተጠርጣሪው የ500 ሺህ ብር ዋስትና ፈቅዷል።

ውሳኔውን ተከትሎም ፖሊስ ይግባኝ ሊጠይቅ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

FanaBC By FanaBC
FanaBC
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 43152
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!