Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
2110 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1710 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1880 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1628 Hits
Read More

Editors Pick

Minilik Assefa
የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ሕገ-መንግሥታዊነት
Constitutional Law Blog
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ መንግሥት የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽንን የሚያቋቁም አዋጅ ማፅደቁ ይታወቃል፡፡ አዋጁ በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ የጦፈ ክርክርን አስነስቶ በ33 ተቃውሞ እና በ4 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ ቢፀድቅም በፓርላማ ውስጥ ለአዋጁ ድምፅ ከነፈጉ የሕዝብ ተወካዮች ጀምሮ እስከ ክል...
11091 hits
Read More
Selam Gebretsion
Extradition regime under The United Nations Convention against Corruption (UNCAC)
Criminal Law Blog
1.      Introduction Globalization is easing border restrictions and increasing travel opportunities. Perpetrators use globalization to avoid prosecution and justice. This problem can be solved by cre...
6786 hits
Read More
Filipos Aynalem
የንግድ ፈቃድን ማከራየት በወንጀል ያስቀጣል?
Commercial Law Blog
በሀገራችን የንግድ ሕግ ሥርዓት መሠረት ነጋዴነት ምን መብቶችና ግዴታዎች አሉበት? ለመሆኑ አንድ ነጋዴ በሥሙ ያወጣውን የንግድ ፈቃድ ለሌላ ሰው ማከራየትና በኪራይ ውል ማስተላለፍ ይችላል? አከራይቶ ቢገኝስ በወንጀል ሊያስከስሰውና ሊያስቀጣው ይችላልን? የነጋዴነት መብቶችና ግዴታዎች በየትኞቹ ህግጋት ይገዛል? የነጋዴዎ...
13230 hits
Read More
Mulugeta Mengist Ayalew (PhD)
‘መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆመ መስሪያ ቤት ላይ’ ግዴታ የሚጥሉ ዉሎች በምን አይነት ቅርጽ መሆን አለባቸዉ?
Contract Laws Blog
መግቢያ የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1724 እንዲህ ይነበባል፤ መንግስት ወይም ለሕዝብ አገልግሎት የቆሙ መስሪያ ቤቶች ግዴታ የሚዋዋሉባቸዉ ዉሎች ሁሉ በጽሁፍና በሚገባ አኳኋን በፍርድ ቤት መዝገብ ወይም ባንድ ባስተዳደር ክፍል መስሪያ ቤት መዝገብ ወይም ዉል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠዉ ሰዉ ፊት መሰራት አለባቸዉ፡፡ እንግ...
11120 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7263 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
218 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
9027 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
408 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
10533 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

ኢትዮጵያ በፔትሮትራንስ ኩባንያ የተመሠረተባትን የ1.4 ቢሊዮን ዶላር ክስ አሸነፈች

 

በፈረንሣይ ፓሪስ በሚገኘው የዓለም አቀፍ ንግድ ምክር ቤት የግልግል ዳኝነት ፍርድ ቤት፣ ፔትሮትራንስ ኩባንያ ሊሚትድ የተሰኘ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የመሠረተው የ1.4 ቢሊዮን ዶላር ክስ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተደመደመ፡፡ የፍርድ ቤት ክርክሩ በጄኔቫ ስዊዘርላንድ ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲካሄድ ቆይቶ፣ ፍርድ ቤቱ ሰኞ ጥር 9 ቀን 2008 ዓ.ም. ውሳኔ መስጠቱን ከታመኑ የዜና ምንጮች ለማወቅ ተችሏል፡፡

ኢትዮጵያ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በኦጋዴን የሚገኙ የነዳጅና የጋዝ ብሎኮችን ፔትሮትራንስ ሊሚትድ ለተሰኘ ኩባንያ ከአራት ዓመታት በፊት በአምስት ስምምነቶች መሠረት ስለመስጠቷ፣ ኩባንያውም በገባው ውል መሠረት ግዴታዎቹን ሊወጣ ባለመቻሉ አምስቱም የነዳጅ ፍለጋ፣ ምርትና ክፍፍል ስምምነቶች በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት ስለመሰረዛቸው፣ ይህንኑ የውሎች መሰረዝ አስመልክቶ የፔትሮትራንስ ኩባንያ ሊሚትድ የኢትዮጵያ መንግሥትን በፓሪስ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ስለመክሰሱና ክርክሩም በመካሄድ ላይ ስለመሆኑ፣ በሪፖርተርና  በተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ጭምር መዘገቡ ይታወሳል፡፡

የዜና ምንጮች እንደጠቆሙት ፔትሮትራንስ ኩባንያ ሊሚትድ ለፓሪሱ ፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ የኢትዮጵያ መንግሥት የሰረዛቸው አምስቱ የነዳጅ ፍለጋ፣ ምርትና ክፍፍል ስምምነቶች ሕገወጥ ናቸው ተብሎ ወደ ሥራው እንዲመለስ እንዲወሰንለት፣ ይህ ካልሆነ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት በጥቅሉ አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሺሕ ዶላር ካሳ እንዲከፈለው ጠይቆ ነበር፡፡   

ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ፍርድ የኢትዮጵያ መንግሥት አምስቱን የነዳጅ ፍለጋ፣ ምርትና ክፍፍል ስምምነቶች የሰረዘው በሕግ አግባብ መሆኑን፣ ፔትሮትራንስ በአማራጭ በኢትዮጵያ መንግሥት እንዲከፈለው የጠየቀው አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሺሕ ዶላር ሊከፈለው እንደማይገባ፣ በክርክሩ ሒደት ኢትዮጵያ ለዳኝነት ያወጣችውን ወጪ ከፊሉን ፔትሮትራንስ ኩባንያ እንዲመልስላት በመፍረድ፣ ኢትዮጵያን በታሪኳ ለቀረበባት ከፍተኛ ክስ ሙሉ በሙሉ አሸናፊ አድርጓታል፡፡

ታዳጊ አገሮች በተለይ የአፍሪካ መንግሥታት በዓለም አቀፍ የንግድና የኢቨስትመንት ፍርድ ቤቶች በሚቀርቡባቸው ክሶች ብዙውን ጊዜ በተሸናፊነት የሚሸኙ መሆኑ ቢታወቅም፣ በኢትዮጵያ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ደረጃ በክሱ መጠን ግዙፍነት በመሪነት በሚጠቀሰው በዚህ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ክርክር፣ ኢትዮጵያ በአሸናፊነት ማጠናቀቋ ለሌሎችም የአፍሪካ መንግሥታት ድል ተደርጎ ሊቆጠር የሚችል ነው ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያን መንግሥት በመወከል የተከራከረው ዓለም አቀፍ የጥብቅና ቢሮ በአሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘውና በቀድሞ መጠሪያው አዲስ ኢንተርናሽናል አርቢትሬሽን ግሩፕ ኤልኤልፒ (Addis International Arbitration Group LLP) የተሰኘው፣ አሁን ደግሞ አዲስ ሎው ግሩፕ ኤልኤልፒ (Addis Law Group LLP) በመባል የሚጠራው ዓለም አቀፍ የጥብቅና ቢሮ፣ ግሪንበርግ ትራውሪግ ኤልኤልፒ (Greenberg Traurig LLP) ከተሰኘውና በዋሽንግተን ዲሲ ከሚገኘው ዓለም አቀፍ የጥብቅና ቢሮ ጋር በመቀናጀት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ፔትሮትራንስ ኩባንያ ሊሚትድን በመወከል የተከራከሩት ዓለም አቀፍ የጥብቅና ቢሮዎች ደግሞ በመጀመርያ ኖርተን ሮዝ ፉልብራይት፣ በኋላ ደግሞ ይህን ቢሮ የተካው ላሊቭ (Lalve) የተሰኘው ዓለም አቀፍ የጥብቅና ቢሮ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የፔትሮትራንስ ኩባንያ ፕሬዚዳንት ጆን ቺን እ.ኤ.አ. በጁላይ 2011 በአዲስ አበባ በሸራተን አዲስ በተካሄደ ሥነ ሥርዓት፣ ከቀድሞዋ የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስትር ወ/ሮ ስንቅነሽ እጅጉ ጋር አምስት የነዳጅ ፍለጋ፣ ምርትና ክፍፍል ስምምነቶች ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ ፔትሮትራንስ ተቀማጭነቱ ሆንግ ኮንግ የሆነ የቻይና ኩባንያ ነው፡፡

Abyssinia Law | Making Law Accessible! By Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 47413
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office