Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
1605 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1346 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1548 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1300 Hits
Read More

Editors Pick

Mulugeta Belay
የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145 አፈፃፀም ላይ የሚስተዋል መሠረታዊ የአሠራር ግድፈት
Criminal Law Blog
በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145 ላይ አንድ ምስክር በፖሊስ ምርመራ ወቅት የሰጠው ቃል ዓቃቤ ሕግ ወይም ተከሳሹ ባመለከተ ጊዜ የተሰጠውን ምስክርነት ፍርድ ቤቱ ሊመለከተው እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ ይህ መብት የተሰጠው ለዓቃቤ ሕግ እና ለተከሳሽ በእኩል ደረጃ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ በሚባል አኳኋን እየተጠቀመ...
17863 hits
Read More
Amare Ayalew Anteneh
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሕገ-መንግሥት መተርጎም ላይ ያለው ሚና እና በጉባዔው አዋጅ ላይ የተደረገ አጭር ምልከታ
Constitutional Law Blog
  መግቢያ ሁሉም ሕጎች በራሳቸው ምሉዕ አይደሉም፡፡ በመሆኑም ሕጎችን በተገቢው የአተረጓጎም ሥርዓት መሠረት ተርጉሞ ሥራ ላይ ማዋል ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ደግሞ አጠቃላይ መርሆዎችን የደነገጉ ሕጎችን የያዙ እንደ ሕገ-መንግሥት ዓይነት ሕጎች በከፍተኛ ጥንቃቄ መሠረታዊ የአተረጓጎም መርሆዎችን በተከተለ ሁኔታ ፍጹም ገለል...
6413 hits
Read More
መንበረጸሐይ ታደሰ (PhD)
The Role of ICT in Judicial Reform in Ethiopia
Others
{autotoc}   Introduction Ethiopia has been implementing justice reform programs for more than 15 years now.  This program is comprehensive and includes all the justice institutions at the federal and ...
6930 hits
Read More
Mulugeta Mengist Ayalew (PhD)
አላግባብ/በስህተት የተከፈለን የጡረታ አበል ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የሚያስቀረዉ የይርጋ ዘመን ምን ያህል ነዉ?
About the Law Blog
መግቢያ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በሰበር ችሎት ዉሳኔዎች ቅጽ 14 መግቢያ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፤ “ለተመሣሣይ ጉዳዮች በጣም የተራራቁ ዉሣኔዎችን በመስጠት ይታይ የነበረዉን ችግር በመቅረፍና የዉሣኔዎችን ተገማችነት በማረጋገጥ ረገድ የሰበር ዉሣኔዎች አስገዳጅ መሆን ከፍተኛ ዉጤት አስገኝቷል ማለት ይቻላ...
9942 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7126 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
164 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
8110 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
350 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
9980 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

እነ አቶ መላኩ ፈንታ የቀረበባቸው ክስ ተሰርዞ እንዲሰናበቱ አቤቱታ አቀረቡ

-ዓቃቤ ሕግ አቤቱታውን ተቃውሞ ምላሽ ሰጥቷል 

-ፍርድ ቤቱ መርምሮ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ሰጠ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው ላለፉት ሁለት ዓመታት በክርክር ላይ የሚገኙትና በክስ መዝገብ 141352 ላይ ከተካተቱት ውስጥ፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታና ሌሎች ተከሳሾች፣ የቀረበባቸው ክስ ተሰርዞ በነፃ እንዲሰናበቱ ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረቡ፡፡ 

በፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ የተመሠረተባቸውን ክስ እየመረመረው ለሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት አቤቱታ ያቀረቡት አቶ መላኩ ፈንታ፣ አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ፣ አቶ በላቸው በየነ፣ አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር፣ አቶ ስማቸው ከበደ፣ አቶ ገብረ ሥላሴ ኃይለ ማርያም፣ ነፃ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ ኮሜት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርና ሌሎችም ናቸው፡፡ 

ተከሳሾቹ ለፍርድ ቤቱ የአቤቱታ ማመልከቻ ያስገቡበትና ክሱ እንዲሰረዝላቸው የጠየቁበት ምክንያት፣ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንን የሚመለከተው አዲስ አዋጅ ቁጥር 859/2006 እነሱ የተከሰሱበትን ክስ ውድቅ እንዳደረገው በመግለጽ ነው፡፡ 

አቶ መላኩ በክስ መዝገብ 141352 ላይ ሦስት ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን፣ የመጀመርያው ለሆቴል አገልግሎት ከቀረጥ ነፃ የገቡ ዕቃዎች ከታለመላቸው ዓላማ ውጪ መዋላቸውን በሚመለከት መረጃ ቢደርሳቸውም፣ ከባለሀብቱ ጋር በመመሳጠር ምርመራ እንዳይጀመርና ለሕግ እንዳይቀርብ አድርገዋል የሚል ነው፡፡ የቀድሞዎቹ አዋጆች፣ አዋጅ 60/89፣ 368/95 እና 622/01 በወንጀል ተጠያቂ የሚያደርጉ ድንጋጌዎች የነበራቸው ቢሆንም፣ በአዲሱ አዋጅ 859/2006 አንቀጽ 181(1) ሙሉ በሙሉ ተተክተው፣ በአንቀጽ 163(1) መሠረት በአስተዳደር ውሳኔ በገንዘብ መቀጮ ብቻ የሚያልቅ እንዳደረገው በመግለጽ አመልክተዋል፡፡ 

ሌላው ቀርቦባቸው የነበረው ክስ ምንም ዓይነት የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ያልተፈጸመባቸው፣ ገደብና ቁጥጥር የተደረገባቸውን 32 ዓይነት ብዛት ያላቸው የተለያዩ ዓይነት የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲገቡ ይያዛሉ፡፡ ክስ ተመሥርቶባቸውና ለፍርድ ተቀጥረው እያሉ፣ ያለ ሕጋዊ ምክንያት ክሱ እንዲነሳ አድርገዋል የሚል ክስ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ይህም ክስ ገደብና ቁጥጥር ከተደረገበት ዕቃ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ በቀደመው አዋጅ ወንጀል የነበሩት ድንጋጌዎች፣ በአዋጅ ቁጥር 859/2006 አንቀጽ 156(1) መሠረት ወንጀልነቱ ቀሪ መሆኑ ቀርቶ በአስተዳደራዊ ውሳኔ በገንዘብ መቀጮ የሚያልቅ መሆኑን ጠቁመው ክሱ እንዲሰረዝ ጠይቀዋል፡፡ 

ሁሉም ተከሳሾች (አቤቱታ ያቀረቡት) እንደ አቶ መላኩ ፈንታ የቀረበባቸው ክስ በአዋጅ ቁጥር 60/89፣ 368/95 እና 622/01 የነበረ መሆኑን በማስታወስ፣ በአዲሱ አዋጅ 859/2006 አንቀጽ 181/(1) መሠረት ሙሉ ለሙሉ የተሻሩ መሆኑን በመጠቆም፣ በተዘረዘሩት ተገቢ አንቀጾች መሠረት የቀረበባቸው ክስ እንዲሰረዝላቸው ጠይቀዋል፡፡ 

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ በሰጠው የአቤቱታ መቃወሚያ መልስ እንዳብራራው፣ እነ አቶ መላኩ ፈንታ የተከሰሱት በወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1)ሀ እና 411 የተመለከተውን በመተላለፍ እንጂ፣ የጉምሩክ አዋጅ አለመሆኑን ገልጿል፡፡ ድንገተኛ ቆጠራ ተደርጐ ባለበት ሁኔታ ድጋሚ ቆጠራ በማስደረግ ቀረጥና ታክስ እንዲቀንስ ያስደረጉ በመሆናቸው፣ ባልተሰረዘ አንቀጽ ክስ እንዲነሳላቸው መጠየቃቸው አግባብ አለመሆኑን ገልጾ፣ አቤቱታው ውድቅ እንዲደረግ ጠይቋል፡፡ 

 

ሌላው ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ የተባሉት ተከሳሽ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ያልተፈጸመባቸውንና ገደብና ቁጥጥር የሚደረግባቸውን 32 ዓይነት የተለያዩ ብዛት ያላቸው የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በአራት ሻንጣዎች በአየር መንገድ ሲያስገቡ መያዛቸውን፣ ክስ ተመሥርቶባቸውና ለፍርድ ተቀጥረው ባለበት ሁኔታ ክሱ እንዲቀር ተደርጎላቸዋል ስለተባለው ዓቃቤ ሕግ ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ዶ/ር ፍቅሩ ዕቃውን በመጀመርያ ሲያስገቡ መስመሩን የተከተለ በመሆኑ ፈቃድ እንዲያቀርቡ መጠየቃቸውን ገልጿል፡፡ ማቅረብ ባለመቻላቸው በሕጋዊ መንገድ ከአገር ዕቃውን እንዲያስወጡ ቢደረጉም፣ በድብቅ መልሰው ሲያስገቡ መያዛቸውን አክሏል፡፡ በዚህ መሠረት በአዋጅ 622/01 አንቀጽ 91(1)ም ሆነ 859/06 አንቀጽ 168(1)ም የኮንትሮባንድ ወንጀል በመሆኑ ሕጉ አለመሻሩን ጠቁሟል፡፡ ዶ/ር ፍቅሩ የተከሰሱት በኮንትሮባንድ ወንጀል በመሆኑ ስለመንገደኞች የዕቃ ዲክለራሲዮን ኦዲትና አቀራረብ የተደነገገውን አንቀጽ 30/2/ለን በመጥቀስ ክሱ እንዲነሳ ማመልከታቸው ከጉዳዩ ጋር አግባብነት የሌለው በመሆኑ አቤቱታው ውድቅ እንዲደረግለት ዓቃቤ ሕግ ጠይቋል፡፡ ዓቃቤ ሕግ ሌሎች ተከሳሾችም ያቀረቡትን ‹‹ክስ ይሰረዝልን›› አቤቱታ በመቃወም ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለግንቦት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ 

EthiopianReporter By EthiopianReporter
EthiopianReporter
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 40395
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office