Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
1794 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1519 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1708 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1460 Hits
Read More

Editors Pick

Abyssinia Law | Making Law Accessible!
የፍርድ ቤቶች በከፊል መዘጋት በማረምያ ቤት ከሚገኙ እስረኞች መብት አንጻር
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
    የኮሮና (COVID-19) በሽታ አለም አቀፍ ችግር ሆኗል፡፡ በአለም ላይ ያሉ ሳይንቲስቶች በደረሱበት የምርምር ደረጃም በትክክል የሚተላለፍባቸው መንገዶች በሙሉ ተለይተው አይታወቁም፡፡ ነገር ግን በሽታው በሰዎች መካከል በሚኖር ቀጥተኝ (መጨባበጥ፤ መተቃቀፍ..) እና ቀጥተኛ ያልሆነ (አንድ ሰው የነካውን ግኡዝ ...
5019 hits
Read More
Michael Teshome
Appeal and arbitration under Ethiopian Arbitration Law
Arbitration Blog
What would you answer if you are confronted with a question: is appeal a fundamental right? Would you say yes, no or neither? I think the argument leans towards yes, does not it? Art 20(6) of the cons...
14637 hits
Read More
Fekadu Andargie Mekonnen
በገጠር መሬት የመጠቀም መብትን በዋስትና ማስያዝና አርሶ አደሩ
Property Law Blog
  መሬት ካለው ተፈጥሮዋዊ ባሕርይም ሆነ ግዙፍነት የተነሳ በሃገራችን ፖለቲካል ኢኮኖሚ ማዕከል ሆኖ እስካሁን ዘልቋል፡፡ በተለይም አብዛኛው ሕዝብ በእርሻ  የሚተዳደር ባለበት ሃገር የመሬት ጉዳይ የኢኮኖሚያዊ መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ የሆነ ጠቀሜታ አለው፡፡ የሃገሪቱን የመሬት ስሪት (land tenure) ወደ ኋላ...
28182 hits
Read More
Mubarek Leulseged
ስለ እንደራሴ (ውክልና) ሕግ አንዳንድ ነጥቦች
About the Law Blog
   ውክልናን የተመለከተው ሕግ በአገራችን በብዛት ስራ ላይ ከሚውሉ የሕግ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የፍትህብሄር ሕግ ቁጥር 2199 ውክልናን እንደተረጐመው “ውክልና ማለት ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ህጋዊ ሥራዎች በወካዩ ሥም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል...
27788 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7210 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
187 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
8541 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
370 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
10258 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

የታገዱ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎች እንዲወዳደሩ የአማራ ክልል ሰበር ሰሚ ትዕዛዝ ሰጠ

-የፓርቲው ሊቀመንበር ፓስፖርታቸው ተመለሰላቸው

በአማራ ክልል በአምስት የምርጫ ወረዳዎች እንዳይወዳደሩ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ተሰጥቶባቸው የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪዎች፣ ውሳኔው ተሽሮ እንዲወዳደሩ መጋቢት 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ትዕዛዝ መሰጠቱ ታወቀ፡፡

ትዕዛዙን የሰጠው አምስት ዳኞች የሚሰየሙበት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሲሆን፣ ከአምስቱ ዳኞች አንደኛው በትዕዛዙና ውሳኔው ተለይተዋል፡፡ ጉዳዩን እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት በማድረስ ያሸነፈው ሰማያዊ ፓርቲ፣ በአማራ ክልል በመርዓዊና በገርጨጭ አምስት የምርጫ ወረዳዎች አምስት ለፓርላማና አሥር ደግሞ ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ያቀርባል፡፡ የቀረቡት ዕጩዎች አባሎቹ መሆናቸውን በመግለጽ ለክልሉ ምርጫ ቦርድ ጽሕፈት ቤት አቤቱታ በማቅረብ እንዲሰረዙ ያደረገው ደግሞ፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ነው፡፡

በዕጩዎቹ መሰረዝ ቅር የተሰኘው ሰማያዊ ፓርቲ ለአማራ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ በመመሥረት ዕጩዎቹ የራሱ መሆናቸውን ያስረዳ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ክሱን መርምሮ በሰጠው ውሳኔ፣ አንድነት ያቀረበው አቤቱታ ትክክል መሆኑን በመደገፍ መሰረዛቸው አግባብ መሆኑን አረጋግጦ ነበር፡፡

የክልሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ያቀረበ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ትክክለኛ ውሳኔ መሆኑን በመግለጽ አፅንቶ ይመልሰዋል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ተስፋ ሳይቆርጥ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ በማቅረቡ፣ የሰበር ሰሚው ችሎት፣ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔን አስቀርቦ የውሳኔ መዝገቦችን መርምሯል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የተወሰነበት ውሳኔ በሕገ መንግሥቱና በተለያዩ የበታች ሕጎች የተደነገገለትን መብት ያጓደለ መሆኑን ጠቅሶ አቤቱታውን አቅርቧል፡፡ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ተሰይመው የሰጡት ውሳኔ ሕጋዊ አለመሆኑን በመዘርዘርም፣ የተሰጠው ውሳኔ ተሽሮ ለውድድር ያቀረባቸው ዕጩዎች መወዳደር እንዲችሉ መጠየቁን የሰበር ሰሚው ችሎት ውሳኔ ያስረዳል፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ በሰበር ችሎቱ ቀርቦ ባደረገው ክርክር ደግሞ፣ ለሰማያዊ ፓርቲ አባል በመሆን ዕጩ ተወዳዳሪ ሆነው የቀረቡት አባላት የአንድነት አባል የነበሩና በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ የተቀመጠውን አስገዳጅ ድንጋጌ ሳያከብሩ ወጥተው፣ ለሰማያዊ ፓርቲ ሊወዳደሩ እንደማይችሉ አስረድቷል፡፡ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ትክክል መሆኑን ገልጾ ውሳኔው እንዲፀናለት ጠይቋል፡፡

ሰበር ሰሚ ችሎቱ የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ መዝገቡን ሲመረምር፣ አንድነት ፓርቲ ሰበር ሰሚ ችሎቱ ጉዳዩን የማየት ሥልጣን እንደሌለው ያቀረበውን መቃወሚያ፣ በክልሉ የሚሰጥን ማንኛውንም ውሳኔ በሚመለከት በመጨረሻ የማየት ሥልጣን እንዳለው በመግለጽ ውድቅ አድርጎበታል፡፡

የመምረጥና መመረጥን ጉዳይ በሚመለከት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 38 እና በምርጫ አዋጅ ቁጥር 573/2000 መሠረት ሰማያዊ ፓርቲ የራሱ መሆናቸውን የገለጻቸው ዕጩዎች፣ ከአንድነት ፓርቲ መምጣታቸውን አለመካዱን ገልጿል፡፡ ነገር ግን ዕጩዎቹ የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆኑት አሁን ሕጋዊ ዕውቅና አግኝቶ በመሳተፍ ላይ ካለው አንድነት ፓርቲ ሳይሆን፣ ለሁለት ተከፍሎ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና ሲጠይቁ ከነበሩትና ዕውቅና የተነፈገው የአንድነት ፓርቲ አባላት የነበሩ መሆኑን ሰማያዊ ፓርቲ ካቀረባቸው ሰነዶቸች መረጋገጡን አስፍሯል፡፡ በመሆኑም አንድነት አባሎቹ እንደሆኑ በመግለጽና የፓርቲውን ሕገ ደንብ እንዳላከበሩ ተደርጎ እንዲታገዱ ያደረገበት አካሄድ ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል፡፡

አንድነት አባሎቹ እንደሆኑ አድርጎ ቢወስድ እንኳን፣ አዋጅ ቁጥር 573/2000 አንቀጽ 31(3) በማንኛውም ጊዜ ያለ ቅድመ ሁኔታ አባልነትን መተው የሚቻል መሆኑን፣ የፓርቲዎች መተዳደሪያ ደንብም አዋጁን መፃረር እንደማይገባው በንዑስ አንቀጽ (4) መደንገጉን ጠቁሟል፡፡ 

የሰማያዊ ፓርቲን ደንብ የተመለከተው ሰበር ሰሚ ችሎቱ በደንቡ አንቀጽ 5.3 ላይ የአንድን ሰው አባልነት ለመቀበል ስድስት ሳምንታትን መጠበቅ እንዳለበት እንደሚገልጽና የአንድነት አባላት ናቸው የተባሉትን ሰዎች ባስቀመጠው ጊዜ ውስጥ መቀበሉን እንደሚያሳይ ጠቁሞ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ‹‹ስድስት ሳምንታቱን አልጠበቀም›› በማለት ያስተላለፈው ውሳኔ ስህተት መሆኑን ገልጿል፡፡ በመሆኑም በሥር ፍርድ ቤቶች ለአንድነት ፓርቲ የተሰጡት ውሳኔዎች መሻራቸውን በመግለጽ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎች በመርዓዊና በገርጨጭ ምርጫ ወረዳዎች እንዲወዳደሩ ወስኗል፡፡ ለመወዳደር የሚከለክላቸው ነገር ስለሌለና ለዕጩነት ብቁ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤትና የምርጫ ወረዳዎቹ እንዲያስፈጽሙ አዟል፡፡ 

በውሳኔውና በትዕዛዙ የተለዩት የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ዳኛ በእንግሊዝ ተፎካካሪ ፓርቲ የሆነውን የሌበር ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ጠቅሰው፣ አንድ የፓርቲ አባል ፓርቲውን ሲለቅ ከ14 ቀናት ላላነሰ ጊዜ ማስታወቂያ ሳይለጠፍ፣ ለሌላ ፓርቲ አባል መሆን እንደማይችል ጠቁመዋል፡፡ በርካታ የአውሮፓ አገሮችም የምርጫ ሥነ ምግባርን ለመዳኘት የሚያስችል ‹‹Anti-Jumping or Anti-Defecting Law›› የሚባል ሕግ እንዳላቸው ጠቅሰው፣ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ አባል እንዴት አባል እንደሚሆንና እንዴት እንደሚተው የሚደነግግ መሆኑን አክለዋል፡፡ አስቀድሞ አባል ለነበሩበት ፓርቲ ማሳወቅ እንዳለበትም እንደሚደነግግ አስረድተዋል፡፡ የአውሮፓ ሰብዓዊ መብት ኮንቬንሽንም ‹‹European Convention on Human Right›› ፓርቲዎች አዲስ አባላትን እንዴት እንደሚቀበሉና እንደሚያጣሩ የሚያስረዳ መተዳደሪያ ደንብ ሊኖረው እንደሚገባ አካቶ እንደሚገኝ ጠቃቅሰዋል፡፡ የዓለም አቀፍ ተሞክሮን ከጠቃቀሱ በኋላ የምርጫ አዋጅ ቁጥር 573/2000 አንቀጽ 31(1) እና ንዑስ አንቀጽ (4) ድንጋጌ ትክክለኛነትንም አረጋግጠዋል፡፡ ነገር ግን አንድ የፓርቲ አባል አባልነቱን በፈቃዱ ሲተው፣ አባል ለነበረበት ፓርቲ እንዲያሳውቅ የሚደነግግ ቀላል የመተዳደሪያ ደንብ በፓርቲዎች እንዳይወጣ የሚከለክል አለመሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተለዩት ዳኛ ሰፋ ያለ ትንታኔ ሰጥተው ዕጩዎቹን በዕጩነት ያቀረቧቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች የሙሉ አባልነት ማዕረግ በሕጉ አግባብ ያገኙ አለመሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በአዋጅ ቁጥር 532/99 አንቀጽ 41(1) እና 46(1) መሠረት መሥፈርት ያላሟሉ ዕጩዎች በመሆናቸው፣ ተቃውሞ ሊቀርብላቸው እንደሚገባም አክለዋል፡፡ በዕጩነት መቅረባቸውም ሕጋዊ ባለመሆኑ እንዲሰረዙ በሥር ፍርድ ቤቶች የተሰጠው ውሳኔ ትክክል መሆኑን ደግፈው ተለይተዋል፡፡ 

ይህ በዚህ እንዳለ መጋቢት 23 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ አሜሪካ ለመሄድ ቦሌ ዓለም  አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፣ በኢሚግሬሽን ሠራተኞች ፓስፖርታቸው መነጠቃቸውን ገልጸው የነበሩት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት፣ መጋቢት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ፓስፖርታቸው እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡ ለምን እንደተነጠቁ ምላሽ የሚሰጣቸው እንዳላገኙ ገልጸው፣ ‹‹ጉልበተኞች ያደረጉትን ያድርጉ እንጂ እኔ አሁንም ለመሄድ እሞክራለሁ፤›› በማለት፣ ሚያዝያ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ አሜሪካ ለመሄድ ማሰባቸውን አስታውቀዋል፡፡ 

EthiopianReporter By EthiopianReporter
EthiopianReporter
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 37923
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office