Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
2110 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1710 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1879 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1627 Hits
Read More

Editors Pick

halefom hailu
የሳይበር ክልልና የሀገሮች የለአላዊነት ስልጣን እስከ ምን ድረስ ለሚለው ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ
Others
አቶ ገብረመስቀል (Gebremeskes Gebrewahd) ወቅታዊ የሆነን ጉዳይ በማንሳትህ ላመሰግንህ እወዳለሁ፡፡ ባነሳኸው ጥያቄ ማለትም የሳይበር ክልል በሃገሮች ሉአላዊነት ላይ ምን ፋይዳ አለው? የሳይበር ክልል መተዳደር ያለበት በሃገራዊ ህግ ነው ወይስ በአለም አቀፍ ህግ? በሚሉ ጉዳዮች ላይ የኔ አስተያየት የሚከተ...
12132 hits
Read More
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
ስለማስረጃ ሕግ አደረጃጀት
About the Law Blog
የማስረጃ ሕግ የማስረጃን አግባብነት፣ የማስረጃን ተቀባይነት እንዲሁም የማስረጃን ክብደትና ብቃት የሚገዙ ደንቦችና መርሆዎች ጥርቅም ነው፡፡ ማስረጃ ተሟጋቾች በአቤቱታቸው አማካኝነት ፍርድ ቤት የያዘውን ጭብጥ የሚያረጋግጡበት ዘዴ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ማስረጃ ማለት ፍርድ ቤት የያዘውን አከራካሪ ጉዳይ ወይም ጭብጥ በ...
15945 hits
Read More
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ፤ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሕግ የማውጣት ሥልጣን እና የአስተዳደሩ ተጠሪነት ጉዳይ
About the Law Blog
    የዚህ አጭር ጽሑፍ ዋና ትኩረቱን በድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/1996 ላይ በማድረግ አዋጁ ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት በአንቀፅ 55(1) ላይ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ከተሰጠው ሕግ የማውጣት ስልጣን ጋር ያለውን ተቃርኖ እና የሕገ መንግስቱን የበላይነት ያላከበረ ...
9607 hits
Read More
Yohannes Eneyew Ayalew
አስገዳጁ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ የሕንጻ መደርመስን ይከላከለው ይሆን?
Construction Law Blog
መግቢያ ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ጉዳይ ልክ የዛሬ አመት ገደማ በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ልዩ ስሙ ሰሚት በሚባል ስፍራ የተደረመሰውን ህንጻ እና እሱን ተከትሎ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደብዳቤ (circular) መሰረት አስገዳጅ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ በድጋሜ እንዲኖር መደረጉን በማስመልከት ነው፡፡ እንደሚታወ...
13863 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7263 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
218 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
9026 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
408 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
10533 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሕግ አግባብ ውጪ ንብረት ሸጧል ተብሎ ክስ ተመሠረተበት

ባዜን እርሻና ኢንዱስትሪ ልማት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ለተበደረው ብድር በመያዣነት ያስያዘውን 10,000 ሔክታር መሬት ከሕግ አግባብ ውጪ በሆነ መንገድ ሸጦብኛል በማለት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ ክስ መሠረተ፡፡

ማኅበሩ ለፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ያቀረበው የፍትሐ ብሔር ክስ እንደሚያስረዳው፣ ባዜን የእርሻና የኢንዱስትሪ ልማት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር ለመበደር ስምምነት ላይ ይደርሳል፡፡ ማኅበሩ ለሚበደረው ገንዘብ በጋምቤላ ክልል አኝዋ ዞን አርፔም ኦፔኖ ወረዳ የሚገኘውን 10,000 ሔክታር መሬት በመያዣነት ይሰጣል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከማኅበሩ ጋር በገባው ውል መሠረት ገንዘቡ ተመላሽ እንዳልተደረገለት (እንዳልተከፈለው) በመግለጽ፣ በቴሌቪዥንና በጋዜጣ የጨረታ ማስታወቂያ በማውጣት በጨረታ መነሻ ዋጋ 35,494,902.40 ብር አወዳድሮ ታኅሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. በ52 ሚሊዮን ብር መሸጡን ክሱ ያብራራል፡፡ ባንኩ በባንክ በመያዥያ ስለተያዘ ንብረት በተደነገገው አዋጅ ቁጥር 97/90 አንቀጽ 5 መሠረት ሊከተላቸው ይገቡ የነበሩ የሕግ ድንጋጌዎች ቢኖሩም፣ የሕግ ድንጋጌውን በመተላለፍ ግዙፍ የሥነ ሥርዓት ግድፈት መፈጸሙን ማኅበሩ በክሱ ዝርዝር አቅርቧል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመያዣነት የያዘውን ንብረት ጨረታ ማውጣት የነበረበት ንብረቱ በሚገኝበት በጋምቤላ ክልል መሆን ቢኖርበትም፣ ጨረታውን ያደረገው ግን የባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት አዲስ አበባ በመሆኑ በአስገዳጅነት የተቀመጡትን የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎችን አለማክበሩን ይጠቅሳል፡፡ አዋጅ ቁጥር 97/90 የአንቀጽ ሁለት ድንጋጌ መሠረት የማይንቀሳቀስን ንብረት በሚመለከት ሬጅስትራር ንብረቱን መመዝገብ እንዳለበት የጠቀሰው ከሳሽ ማኅበር፣ በመያዣነት ያስያዘውን 10,000 ሔክታር መሬት ጨረታ ሲቀርብ እንደ ሬጅስትራር ሆኖ መመዝገብ ያለበት የጋምቤላ ክልል አበቦ ወረዳ አስተዳደር እንደነበር በክሱ ጠቅሷል፡፡ ነገር ግን ባንኩ ጨረታውን አዲስ አበባ በማድረጉ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ጽሕፈት ቤትን የጨረታው ታዛቢ ማድረጉ የአዋጁን መንፈስና ዓላማ የሚጋፋ መሆኑን ጠቅሷል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ52 ሚሊዮን ብር የሸጠውን 10,000 ሔክታር መሬት ማኅበሩ 101 ሚሊዮን ብር ሊሸጠው በመደራደር ላይ እንደነበር በክሱ የጠቀሰ ሲሆን፣ ይኼንኑ ድርድር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደሚያውቅም ጠቁሟል፡፡ በሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ሥር የሚገኘው አግሪ ሴፍት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በ101 ሚሊዮን ብር ሊገዛው እየተደራደረው እንደነበር ባንኩ እያወቀ ጨረታ በማውጣትና ራሱ አግሪ ሴፍት፣ ሳዑዲ ስታር አግሪካልቸዋል ዴቨሎፕመንት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርና የእነሱው አካል ለሆነው አንድ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ የሆኑ ግለሰብ በማጫረት የተፈጸመው የሽያጭ ተግባር ተገቢ ካለመሆኑም በተጨማሪ፣ በማኅበሩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰበት በክሱ ተገልጿል፡፡ 

ማኅበሩ በተደጋጋሚ ጨረታው እንዲሰረዝለት ለንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት ደብዳቤ በመጻፍ ማሳወቁን ጠቁሞ ምላሽ ሊያገኝ አለመቻሉን አስታውቋል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 26553 ከሰጠው አስገዳጅ ትርጉም አኳያ ያቀረበው ክስ ምክንያት ያለው መሆኑን ገልጿል፡፡ በመሆኑም ባንኩ አዋጅ ቁጥር 97/90 (6)ን እና የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ/445ን በመተላለፍ ጉዳት እንዳደረሰበት በመግለጽ ጨረታው እንዲሰረዝለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለቀረበበት የፍትሐ ብሔር ክስ በሰጠው ምላሽ እንደገለጸው፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 84353 በሰጠው አስገዳጅ ትርጉም ባንኩ በመያዣነት የያዘውን ንብረት በሐራጅ ሽጦ ዕዳውን በመሰብሰብ ተግባር ፍርድ ቤቶች ተቀብለው ለማየትም ሆነ ለመወሰን ሥልጣን የላቸውም፡፡ 

ማኅበሩ እንደ ውሉ ግዴታ ባለመክፈሉ በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሽያጩን ያከናወነ በመሆኑ ክሱ ተቀባይነት እንደሌለው በመጥቀስ፣ በቂ ኪሳራ ተቆርጦለት ክሱ ውድቅ እንዲደረግለት ጠይቋል፡፡ ማኅበሩ ከባንኩ 102,258,330 ብር ለመበደር መስማማቱን የጠቆመው ባንኩ በሊዝ በጋምቤላ ክልል ያገኘውን ቦታ የመጠቀም መብት በመያዣነት ማስያዙንም አረጋግጧል፡፡ በማስያዣነት የወሰደውን የሊዝ መብት በአዋጅ ቁጥር 97/90 መሠረት በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት በጨረታ ለመሸጥ የ30 ቀናት ማስጠንቀቂያ መሰጠቱንም ጠቅሷል፡፡ ማኅበሩ በተሰጠው ማስጠንቀቂያ መሠረት ሊከፍለው ባለመቻሉ ሚያዝያ 25 ቀን 2006 ዓ.ም. በጋዜጣና ቴሌቪዥን ጨረታ ቢያወጣም በቂ ተጫራቾች ባለማግኘቱ፣ በድጋሚ ጨረታ አውጥቶ በ52 ሚሊዮን ብር መሸጡን አረጋግጧል፡፡ ጨረታውን ሳዑዲ ስታር አግሪካልቸራል ዴቨሎፕመንት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ማሸነፉንና የሽያጩም ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ለብድር ዕዳው መክፈያነት መዋሉ ንግድ ባንክ አስረድቷል፡፡ 

በክልሉ ማጫረት ሲገባው አዲስ አበባ ማጫረቱን በሚመለከትም ማኅበሩ የጠቀሰው የሕግ ድንጋጌ የሐራጅ ሒደት መከናወን እንዳለበት የሚደነግግ አለመሆኑን ገልጿል፡፡ ማኅበሩ አግሪ ሴፍት በድርድር 101 ሚሊዮን ብር እንደሰጠው የገለጸ መሆኑን ያስታወሰው ባንኩ፣ ከ51 ሚሊዮን ብር በላይ አለማቅረቡን በመግለጽ፣ ማኅበሩ ያቀረበውን ክስ ተገቢና ከአግባብ ውጪ መሆኑን በመዘርዘር ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ ከበቂ ኪሳራ ጋር ከክሱ በነፃ እንዲያሰናብተው በማመልከት ምላሹን አጠቃሏል፡፡ በመያዣነት የተያዘውን 10,000 ሔክታር መሬት በ52 ሚሊዮን ብር እንደገዛው የተገለጸው ሳዑዲ ስታር አግሪካልቸራል ዴቨሎፕመንት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጣልቃ ለመግባት ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል፡፡ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለመጋቢት 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

EthiopianReporter By EthiopianReporter
EthiopianReporter
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 38111
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office