Latest Blog posts
Editors Pick
Latest documents
Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023 7249 Downloads - policies and strategies | 7.6 MB | |
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy 197 Downloads - Arbitration Law | 635.59 KB | |
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25 8781 Downloads - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions | 10.72 MB | |
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED 397 Downloads - Criminal Law | 317.19 KB | |
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25 10408 Downloads - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions | 6.57 MB |
- Details
- Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች
ፍርድ ቤቱ በሃና ላላንጎ የክስ መዝገብ ላይ የአቃቤ ህግን ምስክር ለመስማት ቀጠሮ ያዘ
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ የወንጀል ችሎት የ16 ዓመቷ ሃና ላላንጎን አስገድደው ደፍረው ለህልፈተ ዳርገዋታል በሚል በተጠረጠሩ አምስት ተከሳሾች ላይ የአቃቤ ህግን ምስክር ለመስማት ቀጠሮ ያዘ።
ፍርድ ቤቱ ክስ አሰምቶ መቃወሚያ ካለ ለመቀበል ነበር ቀጠሮ ይዞ የነበረው።
የሟች ቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድና ሌሎች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቀደም ብለው ነው ወደ ፍርድ ቤት የደረሱት።
ችሎቱ ተከሳሾች ላይ የተመሰረተው ክስ ተጣርቶ ለወደፊት ጥፋተኛ ናቸው አይደለም የሚለው ውሳኔ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የተፈፀመው ወንጀል ከሞራልም ሆነ ከሀይማኖት አንፃር ህብረተሰቡ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር ነው ብሏል።
ይህ በመሆኑ እንዲህ አይነት ነገር ሲያጋጥም ህጉ ችሎቱ ዝግ ይሁን ብሎ ስለሚደነግግ በዝግ መሆን አለበት ነው ያለው ፍርድ ቤቱ።
ለችሎቱ ሂደት አስፈላጊ ናቸው የተባሉ አካላት ብቻ ሲቀሩ ጋዜጠኞችን ጨምሮ ሌሎች ታዳሚዎች ችሎቱን በቀጥታ እንዳይከታተሉ ተደርጓል።
ነገር ግን ፍርድ ቤቱ አስፈላጊ የሆነውን ሂደት ብቻ ጋዜጠኞች እንዲያገኙ ባመቻቸው መንገድ መሰረት ተከሳሾች በተመደበላቸው የመንግስት ተከላካይ ጠበቃ አማካኝነት ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።
ተከሳሾቹ ክሱ ተነቦላቸው በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ወንጀሉን አልፈፀምንም ነው ያሉት።
ክደው በመከራከራቸው የአቃቤ ህግ ምስክርን ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለጥር 1፣ 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።