Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
2050 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1658 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1834 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1586 Hits
Read More

Editors Pick

Liku Worku
Analyzing the 'Authority' core feature of Ethiopian Civil Code
Legislative Drafting Blog
How many countries have ‘Codes’ as a basic legal source in the world? In how many countries legal systems the term ‘Codification’ exist? Are there common features of codification used as a basis for c...
12607 hits
Read More
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
የብሮድካስቲንግ ቁጥጥር/ሪጉሌሽን እና የባለሥልጣኑ ደብዳቤ
About the Law Blog
ስለሪጉላቶሪ መሳሪያዎች መግቢያ ዛሬ የብሮድካስቲንግ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ለሁለት ብሮድካስተሮች ጽፈውታል የተባለ ደብዳቤ በፌስቡክ መለጠፉን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየተስተናገዱ ነው። በደብዳቤው ብሮድካስተሮቹ ለምን የቅዳሜውን የድጋፍ ሰልፍ እንዳላስተላለፉ መረጃ በተጠቀሰው ቀን ይዘው በመምጣት ከባለሥልጣ...
9063 hits
Read More
Mamenie Endale
Stolen Asset Recovery in Ethiopia: Critical Legal Issues and Challenges
Commercial Law Blog
Introduction Staling public money hurts the poor disproportionately by diverting funds intended for development, undermining a Government’s ability to provide basic services, feeding inequality and in...
9826 hits
Read More
Yenew B. Taddele
Political risks in construction industry in Ethiopia: who shall bear such risks?
Construction Law Blog
    1. Introduction Risk is part of every human endeavor. From the moment we get up in the morning, drive or take public transportation to get to school or to work until we get back into our beds (and...
6475 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7259 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
203 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
8871 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
403 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
10454 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

ፀረ ሙስና ኮሚሽን ለፓርላማ የቀረበው ረቂቅ የጉምሩክ አዋጅ ድንጋጌዎችን ተቃወመ

-‹‹በዜጎች መካከል ልዩነትን ይፈጥራል›› ብሏል

ከሁለት ሳምንት በፊት ለፓርላማ የቀረበው ረቂቅ የጉምሩክ አዋጅ ውስጥ ‹‹የጉምሩክ ወንጀሎች›› ተብለው የተደነገጉትን አንዳንድ አንቀጾች፣ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ፓርላማ በመገኘት ተቃወመ፡፡

ኮሚሽኑ ረቂቅ ሕጉ ለጉምሩክ ኃላፊ የሚሰጠው ክስ እንዲመሠረት የማድረግ ሥልጣን እንዲሰረዝ ወይም እንዲጠብ በተጨማሪነት ጠይቋል፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት ለፓርላማው ቀርቦ ፓርላማው ለራሱ የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮችና የሕግና ፍትሕ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች ለዝርዝር ዕይታ መርቶት ነበር፡፡ የፀረ ሙስና ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎችም ረቂቅ ሕጉ ላይ ያሉ ድንጋጌዎችን የተቃወሙትና ማስተካከያ ሊደረግባቸው ወይም ሊሰረዙ ይገባሉ ያሏቸውን አንቀጾች ያነሱት፣ የበጀትና የፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በረቂቁ ላይ ባለፈው ሰኞ ባዘጋጀው የባለድርሻ አካላት ውይይት ላይ ነው፡፡

የጉምሩክ ረቂቅ አዋጅ በምዕራፍ ሁለት ድንጋጌው የጉምሩክ ወንጀሎችና ቅጣቶች በሚል ርዕስ ሥር ማንኛውም የጉምሩክ ሹም ወይም የፌዴራል ፖሊስ አባል ወይም በባለሥልጣኑ ሥራ በመተባበር የተሳተፈ ሰው፣ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ወይም በቸልተኝነት አገልግሎቶችን ያጓተተ፣ ዕቃዎች እንዲያዙ፣ ማጓጓዣዎች ከጉዟቸው እንዲስተጓጎሉ ያደረገ ወይም የመሳሰሉትን የፈጸመ ከሆነ ከሦስት ዓመት በማያንስና ከአሥር ዓመት በማይበልጥ እስራት እንደሚቀጣ ያስረዳል፡፡ 

የተሰጠውን ሹመት በግልጽ ተግባር ወይም በግድፈት ያላግባብ የተገለገለና ከተሰጠው ሥልጣን አልፎ የሠራ የጉምሩክ ወንጀል እንደሆነ ተቆጥሮ ከሦስት ዓመት በማያንስና ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እንደሚቀጣ ይገልጻል፡፡

የጉምሩክ ሹም ወይም የፌዴራል ፖሊስ በጉምሩክ ሕጎች የተደነገገውን እንዳይፈጽም ወይም የተከለከለውን እንዲያደርግ መደለያ የሰጠ ወይም መደለያ እንዲሰጥ ወይም እንዲቀበል ያደረገ ማንኛውም ሰው ከሰባት ዓመት በማያንስና ከአሥር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከብር 50,000 በማያንስና ከ100,000 ብር በማይበልጥ መቀጮ እንደሚቀጣ በረቂቁ ተወስቷል፡፡

አቶ ገብሩ ገበየሁ የተባሉ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የሥራ ኃላፊ ረቂቅ ሕጉ ላይ ባለፈው ሰኞ በፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ በተዘጋጀው ውይይት ላይ ተገኝተው፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የረቂቅ አዋጁ አንቀጽ 166 እና 167 ማለትም ከላይ የተዘረዘሩት የወንጀል ዓይነቶች የጉምሩክ ወንጀል ተብለው መቀመጣቸው ተገቢ አለመሆኑን በጽሑፍ ለሚመለከታቸው የሕጉ አመንጪ አካላት ማሳወቁን አስረድተዋል፡፡

ይሁን እንጂ አግባብ አይደለም በሚል በኮሚሽኑ አስተያየት የተሰጠባቸው ሐሳቦች ለፓርላማ በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ባለመካተታቸው የኮሚሽኑን ሥጋት በአካል ለማቅረብ መገኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

‹‹አስተያየታችን መሠረት ያደረገው የሙስና ወንጀልና የጉምሩክ ወንጀል መካከል ልዩነት አልተፈጠረም የሚል ነው፤›› ያሉት የሥራ ኃላፊው፣ በተጠቀሱት አንቀጾች የተቀመጡት ድርጊቶች የሙስና ወንጀሎች ናቸው ብለዋል፡፡ ‹‹አሁንም ቢሆን በሥልጣን ያላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ነው፡፡ በጉምሩክ ሕግ ውስጥ የጉምሩክ ወንጀል ተብሎ የሚታለፍ አይደለም፤›› ብለዋል፡፡ 

ከላይ የተዘረዘሩት ወንጀሎች በሙስና ካልተያዙ የታክስ ሥርዓቱ ላይ ትልቅ አደጋ ነው የሚፈጥሩት ያሉት የሥራ ኃላፊው አቶ ገብሩ፣ በሌሎች የመንግሥት ተቋማት ሥር ያሉ የሥራ ኃላፊዎች ያላግባብ ሥልጣንን መገልገል በሚል በሙስና እየተጠየቁ፣ ይህንኑ ወንጀል የጉምሩክ ሠራተኞች ሲፈጽሙ በጉምሩክ ወንጀል የሚዳኙበት ሥርዓት መፍጠር አግባብነት እንደሌለው አብራርተዋል፡፡

‹‹እንደዚህ ዓይነት ሕግ በዜጎች መካከል ልዩነትን የሚፈጥር ነው፡፡ አንዱ በጉምሩክ ሕግ እንዲዳኝ ሌላው ደግሞ ጠንከር ባለው የሙስና ወንጀል የሚዳኝበትን ሁኔታ ይፈጥራል በማለት አግባብ እንደሌለው በመጠቆም የኮሚሽኑን አቋም ገልጸዋል፡፡

የፀረ ሙስና ኮሚሽን ተወካዩ በተጨማሪ ያነሱት ነጥብ ሙሉ በሙሉ ኮሚሽኑን የሚመለከት ባይሆንም እንደተቋም ግን የሚያገባው በመሆኑ የተሰጠ አስተያየት ነው፤›› ብለዋል፡፡ አስተያየቱ የሚያተኩረው በጉምሩክ ረቂቅ አዋጅ አንቀጽ 150 ላይ የሰፈረውንና ለጉምሩክ ኃላፊ ክስ ያለመመሥረት ሥልጣን የሚሰጠውን ረቂቅ ድንጋጌ ላይ ነው፡፡

በረቂቅ ድንጋጌው መሠረት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የጉምሩክ ወንጀል ፈጽሟል የተባለ ሰው በዕድሜ መጃጀት ወይም በበሽታ ምክንያት ጉዳዩን በፍርድ ቤት መከታተል የማይቻል ከሆነ፣ ጉዳዩ በክስ ሒደቱ ውስጥ ቢያልፍ ብሔራዊ ጥቅምን ወይም ዓለም አቀፍ ግንኙነትን ይጎዳል ብሎ ካመነ ክሱ እንደማይመሠረት ሊያደርግ እንደሚችል ያስቀምጣል፡፡ በተጨማሪም የክሱ መመሥረት ተመጣጣኝና ሚዛናዊ ያልሆነ የጎንዮሽ ጉዳት የሚያስከትል መሆኑ ከታመነበት ወይም ወንጀሉ ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ሳይቀርብ በመቆየቱ አስፈላጊነቱን ያጣ ከሆነ፣ ዋና ዳይሬክተሩ ክስ እንዳይመሠረት ሊያደርግ እንደሚችል በረቂቁ ተመልክቷል፡፡

የኮሚሽኑ ተወካይ ‹‹ክስ እንደማይመሠረት ማድረግ የሚቻልባቸው ሁኔታዎች ሊኖሩ ቢችሉም፣ በጉምሩክ ረቂቅ አዋጅ ላይ የተቀመጡት ምክንያቶች ግን በጣም ልቅ ሆነዋል በመሆኑም ከተቻለ ቢሰረዙ ወይም የሚጠበብት ሁኔታ ቢፈጠር፤›› ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት የግልግል ተቋም ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዮሐንስ ወልደገብርኤልም በዚህ ጉዳይ ላይ ሙያዊ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡ ‹‹በዕድሜ መጃጃት ማለት ምን ማለት ነው? 50 ዓመት ነው? 70 ዓመት ነው? በበሽታ ምክንያት ማለትስ ምን ማለት ነው? በሽታ ማለት ጉንፋን ነው? ወረርሽኝ ነው?›› በማለት ለዋና ዳይሬክተሩ የሚሰጠውን ክስ ያለመመሥረት መብት ለትርጉም ክፍት መሆን አስረድተዋል፡፡ ‹‹በዓቃቤ ሕግ ዓይን ስናየው በዚህ መሥፈርት መሠረት ማንኛውንም ክስ እንዳይመሠረት ማድረግ ይቻላል፤›› ብለዋል፡፡

በተነሱት ሐሳቦች ላይ ምላሽ እንዲሰጡ ዕድል ከተሰጣቸው መካከል ሕጉን በማመንጨት ድርሻ የነበረው የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዋሲሁን አባተ፣ የሙስና ወንጀሎችና የጉምሩክ ወንጀሎች አልተለዩም የሚለውን የፀረ ሙስና ኮሚሽን ሥጋት በተመለከተ በረቂቅ ሕጉ የጉምሩክ ወንጀል እንዲሆኑ የተደረበት ምክንያት ቅጣቱን ጠበቅ ለማድረግ ሲባል ነው ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ሥጋቱ በተደጋጋሚ በመነሳቱ በድጋሚ ለማየት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡ በረቂቅ ሕጉ ላይ የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር ክስ ያለመመሥረት የሚችልባቸውን ጉዳዮች በተመለከተ የተነሳውን የአግባብነት ጥያቄ በተመለከተ፣ ‹‹ክስ የማይመሠረትባቸውን ምክንያቶች እኛ ዝም ብለን አይደለም ያመጣነው፡፡ የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ፖሊሲው ላይ የተቀመጡ ናቸው፤›› ብለዋል፡፡

‹‹የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ፖሊሲው ላይ ክስ ላለመመሥረት በምክንያትነት የተዘረዘሩትን ነው   በረቂቅ የጉምሩክ ሕጉ ላይ እንዲቀመጥ የተደረገው፤›› ያሉት አቶ ዋሲሁን፣ የወንጀል ፖሊሲውን የሚዘረዘርና የሚተነትነው በመዘጋጀት ላይ ባለው የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕጉ በመሆኑ፣ ሥነ ሥርዓቱ ሲሻሻልና ሲፀድቅ መጃጀት ማለት ምን ማለት ነው? በሽታ ማለት ምን ማለት ነው? የሚሉትና ሌሎቹ ምክንያቶቹም ይዘረዘራሉ በማለት መፍትሔውም በዚያ ወቅት እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ውይይቱን ያዘጋጀው የፓርላማው የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከውይይቱ ያገኛቸውን ሐሳቦች ጨምቆ ፓርላማው ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ለእረፍት ከመበተኑ በፊት አዋጁ እንዲፀድቅ ለፓርላማው ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ 

EthiopianReporter By EthiopianReporter
EthiopianReporter
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 34144
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office