Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
2110 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1710 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1879 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1628 Hits
Read More

Editors Pick

Michael Teshome
Period of Limitation, Lapse of a Morgage Vs Art 3058 of the Civil code
About the Law Blog
In 2002, when I was doing my undergraduate degree, our contract law teacher started talking about period of limitation and its effect. I neither had a concept nor an argument about period of limitatio...
9103 hits
Read More
halefom hailu
የሳይበር ክልልና የሀገሮች የለአላዊነት ስልጣን እስከ ምን ድረስ ለሚለው ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ
Others
አቶ ገብረመስቀል (Gebremeskes Gebrewahd) ወቅታዊ የሆነን ጉዳይ በማንሳትህ ላመሰግንህ እወዳለሁ፡፡ ባነሳኸው ጥያቄ ማለትም የሳይበር ክልል በሃገሮች ሉአላዊነት ላይ ምን ፋይዳ አለው? የሳይበር ክልል መተዳደር ያለበት በሃገራዊ ህግ ነው ወይስ በአለም አቀፍ ህግ? በሚሉ ጉዳዮች ላይ የኔ አስተያየት የሚከተ...
12133 hits
Read More
Gizachew Girma Degefu
የሕዝብ ተሳትፎ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ያለው ሚና
About the Law Blog
    1. መግቢያ ቀደም ባሉት ጊዜያት የፍትሕ ሥርዓት ቅቡልነት እና የሕዝብ አመኔታ መሠረት ተደርገው የሚወሰዱት ቢሮክራሲ፣ ምክንያታዊነት እና ሞያን መሠረት ማድረግ ነበር፡፡ በመሆኑም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ዋና ተዋናዮች የሕግ ባለሞያዎች እና ሌሎች የፍትሕ አካላት ባለሞያዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ማህበረሰብ አካላትን ያገለለ...
9776 hits
Read More
Hawi Asfaw
Birth registration and rights of the child
About the Law Blog
{autotoc}   1 Introduction Birth registration is defined as the ‘official recording of a child’s birth by the State’. It is also a lasting and official record of a child’s existence, which usually inc...
7636 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7263 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
218 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
9026 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
408 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
10533 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

ከፀደቀ ሁለት ዓመት የሆነው የኢንቨስትመንት አዋጅ ተሻሻለ

-አዋጁ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ ሥልጣን ይሰጣል 

-ለውጭ ባለሀብቶች የተከለከሉ ዘርፎች እንዳስፈላጊነቱ ሊፈቀዱ ይችላሉ

በ2004 ዓ.ም. ፀድቆ ሥራ ላይ የዋለው የኢንቨስትመንት አዋጅ ከሁለት ዓመት አገልግሎት በኋላ በድጋሚ ተሻሻለ፡፡

አዋጁ ካካተታቸው ማሻሻያዎች መካከል በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ የሚገኘውን የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ወደ ኮሚሽንነት ማሳደግ፣ የኮሚሽኑ የበላይ የሆነ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ማቋቋም ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም የኢንዱስትሪ ልማት ቀጣና መቋቋም የሚቻልበትን ድንጋጌ ማሻሻያው አካቷል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ቀጣና በማለት ሲያብራራ የኢንዱስትሪ ዕድገትን፣ የአካባቢ ብክለት ተፅዕኖ መቀነስንና የከተሞች ዕድገትን በዕቅድና በሥርዓት የመምራት ዓበይት ዓላማዎችን የያዘ መሆኑን አዋጁ ያስረዳል፡፡ 

በተጨማሪም የኢንዱስትሪ ልማት ቀጣና ከላይ የተጠቀሱት ዓላማዎችን ለማሳካት እንደ መንገድ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ውኃና የመሳሰሉ መሠረተ ልማቶችና የተለያዩ አገልግሎቶች ተሟልተውለትና ልዩ የማበረታቻ ዕቅድ ኖሮት አንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይ ወይም ተመጋጋቢነት ያላቸው ኢንዱስትሪዎችን ለማልማት የሚቋቋም ድንበር የተበጀለት ቦታ እንደሚሆን ያስረዳል፡፡ በውስጡም ልዩ የኢኮኖሚ ቀጣና፣ የቴክኖሎጂ ፓርክ፣ የኤክስፖርት ማቀነባበርያ ቀጣና፣ ነፃ የንግድ ቀጣናንና የመሳሰሉትን እንደሚጨምር አዋጁ ያብራራል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ቀጣናን ማልማት ወይም ማቋቋም የሚችሉት የፌደራል መንግሥት ወይም አስፈላጊነቱ ሲታመንበት በመንግሥትና በግል ባለሀብቶች ቅንጅት ወይም በግል ባለሀብቶች ሊለማ እንደሚችል በአዋጁ ድንጋጌ ተካቷል፡፡

በሥራ ላይ የሚገኘው የኢንቨስትመንት አዋጅ በአገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ የሚካሄዱ የሥራ መስኮች በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ እንደሚወሰኑ የሚገልጽ ሲሆን፣ ቀጥሎ በወጣው ደንብ መሠረትም ለኢትዮጵያ ባለሀብቶች ብቻ ተብለው የተከለሉ የሥራ መስኮችን ይዘረዝራል፡፡

በዚህም መሠረት የባንክ፣ የኢንሹራንስና አነስተኛ የብድርና ቁጠባ ተቋም ሥራዎች፣ ዕቃዎችን የማሸግ፣ የማስተላለፍና የመረከብ ውክልና አገልግሎቶች፣ የብሮድካስቲንግ አገልግሎትና የመገናኛ ብዙኃን ሥራዎች፣ የጥብቅናና የሕግ ማማከር አገልግሎት፣ አገር በቀል ባህላዊ መድኃኒቶችን ማዘጋጀት፣ የማስታወቂያ፣ ፕሮሞሽንና የትርጉም ሥራዎች መሆናቸውን ይገልጻል፡፡

በኢንቨስትመንት አዋጁ ላይ በተደረገው ማሻሻያ ግን ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ የተከለሉ የሥራ መስኮች አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ለውጭ ባለሀብቶችም ክፍት እንዲሆኑ ኮሚሽኑ ሊፈቅድ እንደሚችል ያስረዳል፡፡

የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ቦርድ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራ ሲሆን፣ የኢንዱስትሪ ቀጣናዎች አስተዳደርና ቁጥጥርን በበላይነት መምራትና የኢንዱስትሪ ልማት ቀጣናዎች ስለሚሰየሙበት አሠራር፣ ስለሚመደቡባቸው መሥፈርቶች፣ ስለድንበራቸው አወሳሰን፣ በቀጣናዎች ውስጥ ስለሚሰማሩ ባለሀብቶች መብትና ግዴታ፣ በኢንቨስትመንት አዋጁ መሠረት ከሚያገኟቸው ማበረታቻዎች በተጨማሪ ስለሚያገኟቸው ማበረታዎችና ሌሎችም ጉዳዮች ቦርዱ መመርያ የማውጣት ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡

አዋጁ ከመፅደቁ በፊት የፓርላማው የኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎችን በመጥራት ባካሄደው ውይይት፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ኮሚሽኑ መሥራት የሚገባቸውን የኢንቨስትመንት ተግባራትን የማስፈጸምና መመርያዎችን የማውጣት ሥልጣን ለምን እንደተሰጠው ማብራርያ ጠይቆ ነበር፡፡

‹‹ለአብነት ያህል በኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ አንድ ትልቅ የፋርማሲዩቲካል ኩባንያ ቢመጣና ኢትዮጵያን ማዕከል አድርጌ ወደ አፍሪካ መላክ ስለምፈልግ የመሬት ሊዝ ዋጋ በዚህን ያህል ብር ስጡኝ፣ የተቀመጠው ማበረታቻ አይበቃኝም ቢልና ሌሎች ጉዳዮችን ቢያነሳ እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚሰበስበው ቦርድ መወሰን እንደሚገባው ለማድረግ ነው፡፡ እንደ ሁኔታው ምላሽ እየተሰጠ ባለሀብቱን መያዝ ካልተቻለና ሁሉንም በአንድ ዓይነት ሁኔታ እናስተናግድ ከማለት ይልቅ፣ የሚያስፈልግ ከሆነ ላላ በማድረግ ከፖለቲካውም አንፃር አይቶ ማቀላጠፍ ካልተቻለ ውጤቱ አመርቂ እንደማይሆንና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እንደማይቻል በማሰብ ነው፤›› በማለት ምሳሌ አዘል ማብራርያ ተሰጥቷል፡፡

በማሻሻያ አዋጁ ላይ በኢንዱስትሪ ቀጣና ልማት ውስጥ ከሚካተቱት መካከል ነፃ የንግድ ቀጣና ትርጓሜ ግልጽ እንዲሆንለት ቋሚ ኮሚቴው በጠየቀው መሠረት፣ ‹‹በአንድ የተከለለ ቦታ ዕቃዎች ከውጭ ገብተውና በምርት ሒደት ውስጥ አልፈው ቁጥጥር ከተደረገባቸው በኋላ ወደ ውጭ የሚወጡበት ሒደት ነው፤›› በማለት የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች አብራርተዋል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው አስፈላጊውን ማጣሪያና የማሻሻያውን አስፈላጊነት በመፈተሽ፣ ባለፈው ሐሙስ ለፓርላማው በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ መሠረት ማሻሻያው በሙሉ ድምፅ ፀድቋል፡፡  

EthiopianReporter By EthiopianReporter
EthiopianReporter
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 34780
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office