Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
1793 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1519 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1708 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1460 Hits
Read More

Editors Pick

Betru Dibaba
Constitutional Special Interest of the State of Oromia in Addis Ababa City Administration
Constitutional Law Blog
INTRODUCTION         The phraseology of special interest is technical employment. The geographical location, historical, socio economic underpinnings and legal grounds attract the attention of ONRS an...
29387 hits
Read More
Sentayehu Getachew
የረዳት አብራሪው ኃይለመድህን አበራ የወንጀል ክስ ጉዳይ በየትኛው አገር ፍ/ቤት መታየት አለበት?
Criminal Law Blog
ፌቡራሪ 17/2014 እ.ኤ.አ. ዕለተ ሰኞ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ በበረራ ቁጥር ET 702 የተመዘገበ ቦይንግ 767 የመንገደኞች ማመላለሻ አውሮፕላን ከአዲስ አበባ በሱዳን በኩል አድርጎ ወደ ጣሊያን ሲበር በረዳት አብራሪው ሃይለመድህን አበራ ተገድዶ ስዊዘርላንድ ጄኔቭ ማረፉን ተከትሎ የስዊዘርላንድ...
13833 hits
Read More
Mulugeta Belay
የዜግነት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ የቅድመ ሁኔታዎቹ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ:- ለአቶ ግዛው ለገሰ የተሰጠ ምላሽ
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
    ስለ ዜግነት አዎጁ በፃፍኩት ጽሑፍ ላይ አቶ ግዛዉ ለገሰ የተባሉ የሕግ ባለሙያ የፃፉት ምላሽ ደርሶኝ ተመለከትኩት፡፡ (የአቶ ግዛው ለገሰ ጽሑፍን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ፡፡ ) በመጀመሪያ ጸሐፊው የሕግ ባለሙያ እንደመሆናቸውም ብሎም ጽሑፉን ያወጡት እሳቸው ስላልተስማሙበት የሕግ ጽሑፍ ምላሽ ለመስጠት እንደ መሆኑ...
7418 hits
Read More
Liku Worku
Modernizing the Legislative and Regulatory Framework of Ethiopia
Legislative Drafting Blog
  Prior to considering the subject matter of this article, a brief explanation of the history of Ethiopian Codes and constitutional development is helpful because it focus attention to the key issues ...
13480 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7210 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
187 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
8541 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
370 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
10258 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

በተመሳሳይ የወንጀል ጥርጣሬ የተለያየ ትዕዛዝ የተሰጠባቸው ጋዜጠኞችና ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ

‹‹ከተደጋጋሚና አሰልቺ ‘አባል ነህ?’ ጥያቄ ውጪ ምንም አልተጠየቅንም›› ተጠርጣሪ ጋዜጠኞች

በህቡዕ በመደራጀት፣ ሥልጠና በመውሰድና በውጭ ከሚገኙ አሸባሪዎች ጋር በመገናኘት የአመፅ ወንጀል ለመፈጸም ሲቀሳቀሱ ነበሩ ተብለው የተጠረጠሩት ጋዜጠኞችና ጦማርያን ላይ ፍርድ ቤት የተለያዩ ትዕዛዞች ሰጠ፡፡  

በቁጥጥር ሥር ከዋሉ 26 ቀናት ያስቆጠሩት ተጠርጣሪዎቹ ለሦስተኛ ጊዜ በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ግንቦት 9 እና 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀርበዋል፡፡ ግንቦት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. የቀረቡት ተጠርጣሪ ጋዜጠኞች ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና ኤዶም ካሣዬ ሲሆኑ፣ ጦማርያኑ ደግሞ መምህር ዘላለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፍ ብርሃን ናቸው፡፡ 

ተጠርጣሪዎቹ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የደረሱ ሲሆን፣ እነሱ ከመድረሳቸው በፊት የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ቀደም ብለው ፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ በመድረስ፣ የተጠርጣሪዎቹን መምጣት ይጠባበቁ የነበሩ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የተለያዩ ኤምባሲዎች ዲፕሎማቶችና ሌሎችን ወደ አንድ ጥግ ተሰብስበው እንዲቆሙ አደረጉ፡፡

ሁለት ሌሎች ተጠርጣሪዎችን ተከትለው ወደ ችሎቱ የገቡት ኤዶም፣ ናትናኤልና አጥናፍ ናቸው፡፡ ናትናኤልና አጥናፍ ፊታቸውን ቅጭም እንዳደረ የታሰሩበትን ሰንሰለት እያዩና በታሰረ እጃቸው ሰላምታ በሚመስል መልኩ ወደ ጐን ወደ ሕዝቡ እያዩ ወደ ውስጥ ዘለቁ፡፡ ከእያንዳንዳቸው ሦስትና ሁለት ቤተሰብ እንዲገባ ተፈቅዶ ችሎቱ ሥራውን ጀመረ፡፡ 

ችሎቱን ከታደሙትና ከተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ የዕለቱን የምርመራ ሒደት ለመረዳት እንደተቻለው፣ የፌዴራል መርማሪ ቡድን ያካሄደውን የምርመራ ውጤት እንዲያስረዳ ፍርድ ቤቱ ጠይቆታል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በህቡዕ በመደራጀት በሕጋዊ መንገድ ሥልጣን የያዘውን መንግሥት በሕገወጥ ሁኔታ ለማስወገድ በማሰብ፣ በውጭ አገር ከሚገኙ አሸባሪዎች ጋር በመስማማት አገሪቱንና ሕዝቡን ለማተራመስ ገንዘብና ትዕዛዝ በመቀበል፣ ሥልጠና በመውሰድ፣ ብጥብጥ ለማስነሳትና ለመምራት፣ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም መንቀሳቀሳቸውን የሚያሳይ ፍንጭ ማግኘቱን ማስረዳቱን የችሎቱ  ታዳሚዎቹ ገልጸዋል፡፡ በመቀጠልም፣ ዓቃቤ ሕግ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራ መቀጠል ያለበት የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ሳይሆን፣ በፀረ ሽብርተኝነት ሕግ አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 28 መሠረት መሆኑን በማስረዳት ለምርመራ ጊዜ 28 ቀናት እንዲፈቀድለት መጠየቁንም አስረድተዋል፡፡

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በበኩላቸው ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ መርማሪ ቡድኑ ከዕለቱ ችሎት በፊት ሁለት ጊዜ አቅርቧቸዋል፡፡ ለፍርድ ቤቱም ያስረዳው ለጥርጣሬው ምክንያት የሆነው ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ ድረ ገጾች ላይ ኅብረተሰቡን ለአመፅ የሚያነሳሱ መጣጥፎችን መጻፋቸውን እንጂ ስለሽብር ያለው ነገር እንደሌለ ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት፣ ፍርድ ቤቱ ከመዝገቡ ሊያረጋግጥ እንደሚችል መጠቆማቸውንም አስታውቀዋል፡፡ መርማሪ ቡድኑም 15 ቀናት የምርመራ ተጨማሪ ጊዜ ጠይቆ ፍርድ ቤቱ በወቅቱ አሥር ቀናት ብቻ እንደሚበቃው በማመኑ አሥር ቀናት ብቻ ፈቅዶለት እንደነበር የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ ማስረዳታቸውን አክለዋል፡፡

ጠበቃ አመሐ መኰንን ተጠርጣሪዎቹን ለአንድ ቀንና ለአጭር ጊዜ አግኝተው ሲጠይቋቸው፣ መርማሪዎች በተደጋጋሚ የሚጠይቋቸው አንድ ዓይነትና ‹‹የዞን 9 አባል ነህ›› የሚል ብቻ መሆኑን ጠቅሰው፣ ስለሽብርተኝነት ምንም ዓይነት ጥያቄ ቀርቦላቸው እንደማያውቅ እንደነገሯቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድተው፣ ‹‹መርማሪ ቡድኑ ምርመራዬን የምቀጥለው በሽብርተኝነት ሕጉ ነው፤›› ማለቱን መቃወማቸውን ገልጸዋል፡፡

ሥልጠና መውሰድን በሚመለከት ጠበቃ አመሐ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት ተጠርጣሪዎቹ ሥልጠና ወስደዋል የተባሉት ‹አርቲክል 19› እና ‹ፍሪደም ሐውስ› በሚባሉ ድርጅቶች መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ድርጅቶቹ በአሜሪካና በእንግሊዝ መንግሥታት ዕውቅና ያላቸው በሽብርተኝነት ያልተፈረጁ ሕጋዊ ድርጅቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ላይ የሚሠሩ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያላቸው ድርጅቶች መሆናቸውን በማስረዳት፣ መርማሪ ቡድኑ ጉዳዩን ወደ ሽብር ለመውሰድ ከመናገር ያለፈ፣ ባለፈው ከመረመረውና ለፍርድ ቤቱ ካቀረበው ውጪ የጨመረው ስለሌለ ደንበኞቻቸው ዋስትና ተጠብቆላቸው ከእስር እንዲፈቱ አመልክተዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ የሁለቱንም ወገን ማመልከቻ ካዳመጠ በኋላ፣ መርማሪ ቡድኑ የጠየቀውን የ28 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ በመፍቀድ የስድስቱን ተጠርጣሪዎች ችሎት አብቅቷል፡፡

እሑድ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. የቀረቡት ደግሞ ጦማርያን አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማህሌት ፋንታሁን ናቸው፡፡ ግንቦት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀርበው ለነበሩት ተጠርጣሪዎች መርማሪ ቡድኑ ያቀረበውን ተመሳሳይ የምርመራ ውጤትና ተመሳሳይ የ28 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቋል፡፡ የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃም ከላይ ለተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች ያቀረቡትን መቃወሚያ ካቀረቡ በኋላ ፍርድ ቤቱ የራሱን ጥያቄ ለመርማሪ ቡድኑ አቅርቧል፡፡

ምን አዲስ ነገር በምርመራ መዝገባቸው ላይ እንዳያያዙ መርማሪ ቡድኑ እንዲያስረዳው ፍርድ ቤቱ ጥያቄ ሲያቀርብ፣ መርማሪ ቡድኑ የተጠርጣሪዎቹን የይለፍ ፈቃድ (ፓስ ወርድ) ተቀብሎ የተላላኩትን የኢሜል መልዕክት ሲፈትሽ፣ ከሽብርተኞች ጋር የተጻጻፉትን ማግኘቱን አስረድቷል፡፡ ከመዝገቡ ጋር ግኝቱን አያይዞ እንደሆነ እንዲገልጽ ፍርድ ቤቱ ሲጠይቀው፣ ገና አለማያያዙን በመግለጽ ላይ እያለ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን ሲመለከት፣ ቀደም ብሎ ለጥርጣሬ ያበቃውን ከመጥቀሱ ሌላ ያለው ነገር አለመኖሩን በማየቱ፣ ወደ ሽብር ድርጊት የሚመራ ምክንያት ተጠቅሶ በመዝገቡ ላይ አለመቀመጡን በመግለጽ የተጠየቀውን 28 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ በግማሽ ቀንሶ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ብቻ በመፍቀድ የዕለቱን ችሎት አጠናቋል፡፡ 

Ethiopianreporter By Ethiopianreporter
Ethiopianreporter
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 33711
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office