Latest Blog posts
Editors Pick
Latest documents
Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023 7120 Downloads - policies and strategies | 7.6 MB | |
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy 163 Downloads - Arbitration Law | 635.59 KB | |
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25 8006 Downloads - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions | 10.72 MB | |
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED 350 Downloads - Criminal Law | 317.19 KB | |
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25 9924 Downloads - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions | 6.57 MB |
- Details
- Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች
መኖሪያ ቤት በቡድን የዘረፉ እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች ከ9 እስከ 30 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በግለሰቦች መኖሪያ ቤት ገብተው የጦር መሳሪያ በመያዝ የዝርፊያና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሶስት ግለሰቦች ከ9 እስከ 30 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ።
አቃቢ ህግ በእነአንዳረጌ ጥላሁን የክስ መዝገብ አምስት ግለሰቦችን ነው በከባድ የውንብድና ወንጀል ክስ መስርቶባቸው የነበረው።
ተከሳሸቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ህይወቱ ያለፈው አንደኛ ተከሳሽ የሰሜን ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ነዋሪ የነበረው አንዳረጌ ጥላሁን ፣ የቦሌው ፍስሃ ሻረው ፣ የሰሜን ወሎ ዞን ሳይንት ከተማ ኗሪው ይመኑ አዳነ ፣ የአቃቂ ቃሊቲው መለሰ ሞገስ እና የቦሌው መርጊያ ሽመልስ ናቸው።
በ2003 ዓ.ም ሽጉጥ እና ሌሎች የጦር መሳያዎች ይዘው ቦሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 10 አብሽሮ ህንፃ በሟች ዶክተር መሀሙድ መሀመድ ቤት ነው የውንብድና ተግባራቸውነ አንድ ብለው የጀመሩት።
በዚሁ ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩትን ሰባት ሰዎች እንገላችኋለን በማለት አስፈራርተው እንዳይጮሁ በማስጠንቀቅ የተለያዩ ሞባይሎችን ጨምሮ የአንገትና የጆሮ ወርቆችን የወሰዱ ሲሆን ፥ የቤቱ ባለቤት ዶላር አምጣ ብለውት የለኝም ሲላቸው ከምሽቱ 5 ስዓት ተኩል በሽጉጥ ገድለውት ተሰውረዋል።
በዚሁ ዓመት ከወራት በኋላ ሌላኛው የጥቃት ኢላማቸውን ወ/ሪት ወርቅአበባ በሚባሉ ግለሰብ ቤት አድርገገው ፤ ምሽት ሁለት ስዓት ሲሆን በዚሁ ቤት ኡዚ ጠመንጃና ስታርተር ሽጉጥ ይዘው በመግባት በቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦችን በሰደፍና በዱላ በመደብደብ ጥሬ ብር ፣ የተለያዩ ወርቆችንና የሞባይል ስልኮችን ወስደዋል።
ይህ አልበቃ ብሏቸው ወይዘሮዋን ከደበደቡ በኋላ የሚተኙበትን ፍራሽ ገልብጠው ሽጉጥ እስከነ 12 ጥይቶቹ ወስደዋል።
በዚያው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተሰብ ባርና ሬስቶራንት ውስጥ እየተዝናኑ በማምሸት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ሲሆን ከሌሎች ደንበኞች ጋር ግጭት በመፍጠራቸው ሬስቶራንቱ ይዘጋል ፤ ነገር ግን ተመልሰው በር ሰብረው በመግባት ከ24 ሺህ ብር በላይ ዘርፈው የሬስቶራንቱን ስራ አስኪያጅና ባልደረቦቹን ደብድበዋል ።
በዚህ ክፉ ተግባራቸው ተሰውረው የነበሩ እነዚህ ወንጀለኞችን ፖሊስ ከተሸሸጉበት ይዟቸው በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል።
አቃቢ ህግ ከዚህ በመነሳት በከባድ የውንብድና ወንጀል ክስ በመመስረት ፥ መዝገቡን ሲመረምር የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ የወንጀል ችሎት ክሳቸው ከተቋረጠባቸው አንዳረጌ ጥላሁንና 5ኛ ተከሳሽ መርጊያ ሽመልስ ውጪ ሌሎቹን በእስራት ቀጥቷቸዋል።
በዚህ መሰረት በተደራራቢ ክሶች የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበት የነበረው 2ኛው ተከሳሽ ፍስሃ ሻረው ተደማምሮበት በ30 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል።
ይህ ተከሳሽ ምንም እንኳን ከፍተኛ የወንጀል ተሳትፎ ቢኖረውም በአካል ተገኝቶ ክርክር አድርጎ የቅጣት ማቅለያ ባለማቅረቡ ነው የ30 ዓመት ፅኑ እስራት የተላለፈበት።
ፍርድ ቤቱ በግብር አባሮቹ ኢመኑ አዳነና መለሰ ሞገስ ላይም በእያንዳንዳቸው ላይ የ9 ዓመት ጽኑ እስራት ቅጣት አስተላልፏል።
ፍርድ ቤቱ ፥ በሌለበት ውሳኔ በተሰጠው 2ኛ ተከሳሽ ፍስሃ ሻረውም የፌደራል ፖሊስ አፈላልጎ የእስራት ቅጣቱን እንዲፈፀም አዟል።