Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Federal Laws Database
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • Discussions
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Professional Advice?
    • Contact us
    • How to submit a blog post
  • login
Sesay Goa

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

ዳግም ኢጣሊያ ወረራ ፈፅሞ ለአምስት አመት ግዛቱን ባስተዳደረበት ጊዜና ኢጣሊያን በእንግሊዝ አጋዥነትና በሀገር ውስጥ በነበሩ አርበኞች ያላቋረጠ ትግል ከሀገር ሲባረር ስልጣን በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ቁጥጥር ስር ቢገኝም የእንግሊዝ መንግስት አስተዳደር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ፓሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጣልቃ ገ

Sesay Goa
Criminal Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Fasika Abera

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

በእርግጥ ሁሉም ችግሮች እንደየደረጃቸው እና ጥልቀታቸው በጥናት የሚለዩ መሆኑን አምናለሁ። ይሁን እና ጥናትም ለማድረግ ችግሩ ባለቤት ሊኖረው የሚገባ ስለመሆኑ ደግሞ የምንግባባበት ነው ብየ አስባለሁ። ይህ እንዳለ ሆኖ ጥናትም ለማድረግ ቢሆን መጀመርያ ላይ መነሻ ሊኖረን የሚገባ ነው። ለዚህም ነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተ

Fasika Abera
Human Rights, Public Policy and Law Blog
17 March 2023
Continue reading
Michael Teshome

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

በውሳኔው ሐተታ ላይ ‹‹…ይህ መርህ የግልግል ዳኛው የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ ዋጋ ያለው መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የሚነሳ ክርክር ጭምር ሰምቶ መወሰን እንዲችል ሥልጣን የሚሰጠው ቢሆንም ይህ መርህ… በአገራችን በከፊል ተቀባይነት ባለማግኘቱ በዚህ ድንጋጌ መሠረት በአገራችን የግልግል ዳኛ የግልግል ዳኝነት ስምምነቱ

Michael Teshome
Arbitration Blog
22 February 2023
Continue reading
muluken seid hassen

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ

muluken seid hassen
Family Law Blog
30 December 2022
Continue reading
Nigussie Redae

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

እንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ተቋማት በእጅጉ በግልሰቦች እና በተለያዩ ፖለቲካዊ ተፅዕኖዎች ውስጥ የወደቁ በመሆናቸው የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀም ላይ ብዙ ጥሰቶች ሲፈፀሙ መቆየታቸው ማስረጃ የማይጠየቅበት እውነት ነው። ከእነዚህ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 1

Nigussie Redae
Criminal Law Blog
03 May 2023
Continue reading
Fesseha Negash Fantaye

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Including the abstract, introduction, and concluding remarks, the author’s work is structured into eight sections. The author used abstract and introduction to introduce readers to his work's content,

Fesseha Negash Fantaye
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
22 April 2023
Continue reading

Latest Blog posts

Nigussie Redae
Nigussie Redae
03 May 2023
የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም
Criminal Law Blog
መግቢያ በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በ...
1571 Hits
Read More
Fesseha Negash Fantaye
Fesseha Negash Fantaye
22 April 2023
ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy
Opinion/Critiques/Case Comment/Public Lecture
Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here) The arbitration agreement ...
1314 Hits
Read More
Sesay Goa
Sesay Goa
17 March 2023
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ
Criminal Law Blog
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም ...
1521 Hits
Read More
Fasika Abera
Fasika Abera
17 March 2023
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች
Human Rights, Public Policy and Law Blog
እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።...
1269 Hits
Read More

Editors Pick

Yenew B. Taddele
Effect of Irregularities in Public Contract Awarding
Contract Laws Blog
  {autotoc}     Abstract...
7819 hits
Read More
Muluneh Bayabill Dessie
Legal Aspects of Electronic Commerce: The Case in Ethiopia
Commercial Law Blog
{autotoc}    Introduction The century we are living in is the age of information and communication technology. Increased use of these electronic communications improve the efficiency of commercial act...
12457 hits
Read More
Awel Sultan Mohammod
የእንደራሴነት ሕግ (Agency Law) ዋና ዋና ነጥቦች
About the Law Blog
መግቢያ   ሰዎች ኑሮአቸውን ስኬታማ ለማድረግ በሚፈጽሙት የእለት ተእለት ተግባራቸው ከሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎች ጋር ዘርፈ ብዙ መስተጋብሮችን የሚፈጽሙ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይሁንና እነኚህን መስተጋብሮች  በተለያዩ ምክኒያቶች በራሳቸው ለመፈጸም የማይችሉ በሆነ ጊዜ ሥራዎችን ሌላ ሰው እንዲያከናውንላቸው ፍላጎት ሊያድር...
10569 hits
Read More
muluken seid hassen
ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ
Family Law Blog
በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ህጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማ...
5614 hits
Read More

Latest documents

Education and Training Policy of Ethiopia - Amharic version - 2023
7120 Downloads  - policies and strategies
7.6 MB
The Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration - the Extent of Party Autonomy
163 Downloads  - Arbitration Law
635.59 KB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25
8006 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
10.72 MB
ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ እይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ FEATURED
350 Downloads  - Criminal Law
317.19 KB
Federal Supreme Court Cassation Decisions - Table of content Volume 1-25
9924 Downloads  - Federal Supreme Court Cassation Bench Decisions
6.57 MB
Print Email
Details
Category: Legal News - የሕግ ዜናዎች

መኖሪያ ቤት በቡድን የዘረፉ እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች ከ9 እስከ 30 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ

በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በግለሰቦች መኖሪያ ቤት ገብተው የጦር መሳሪያ በመያዝ የዝርፊያና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሶስት ግለሰቦች ከ9 እስከ 30 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ።

አቃቢ ህግ በእነአንዳረጌ ጥላሁን የክስ መዝገብ አምስት ግለሰቦችን ነው  በከባድ የውንብድና ወንጀል ክስ መስርቶባቸው የነበረው።

ተከሳሸቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ህይወቱ ያለፈው አንደኛ ተከሳሽ የሰሜን ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ነዋሪ የነበረው አንዳረጌ ጥላሁን ፣ የቦሌው ፍስሃ ሻረው ፣ የሰሜን ወሎ ዞን ሳይንት ከተማ ኗሪው ይመኑ አዳነ ፣ የአቃቂ ቃሊቲው መለሰ ሞገስ እና የቦሌው መርጊያ ሽመልስ ናቸው።

በ2003 ዓ.ም ሽጉጥ እና ሌሎች የጦር መሳያዎች ይዘው ቦሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 10 አብሽሮ ህንፃ በሟች ዶክተር  መሀሙድ መሀመድ ቤት ነው የውንብድና ተግባራቸውነ አንድ ብለው የጀመሩት።

በዚሁ ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩትን ሰባት ሰዎች እንገላችኋለን በማለት አስፈራርተው እንዳይጮሁ በማስጠንቀቅ የተለያዩ ሞባይሎችን ጨምሮ የአንገትና የጆሮ ወርቆችን የወሰዱ ሲሆን ፥ የቤቱ ባለቤት ዶላር አምጣ ብለውት የለኝም ሲላቸው ከምሽቱ 5 ስዓት ተኩል በሽጉጥ ገድለውት ተሰውረዋል።

በዚሁ ዓመት ከወራት በኋላ ሌላኛው የጥቃት ኢላማቸውን ወ/ሪት ወርቅአበባ በሚባሉ ግለሰብ ቤት አድርገገው ፤ ምሽት ሁለት ስዓት ሲሆን በዚሁ ቤት ኡዚ ጠመንጃና ስታርተር ሽጉጥ ይዘው በመግባት በቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦችን በሰደፍና በዱላ በመደብደብ ጥሬ ብር ፣ የተለያዩ ወርቆችንና የሞባይል ስልኮችን ወስደዋል።

ይህ አልበቃ ብሏቸው ወይዘሮዋን  ከደበደቡ በኋላ የሚተኙበትን ፍራሽ ገልብጠው ሽጉጥ እስከነ 12 ጥይቶቹ ወስደዋል።

በዚያው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተሰብ ባርና ሬስቶራንት ውስጥ እየተዝናኑ በማምሸት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ሲሆን ከሌሎች ደንበኞች ጋር ግጭት በመፍጠራቸው ሬስቶራንቱ  ይዘጋል ፤ ነገር ግን ተመልሰው በር ሰብረው በመግባት ከ24 ሺህ ብር በላይ ዘርፈው የሬስቶራንቱን ስራ አስኪያጅና ባልደረቦቹን ደብድበዋል ።

በዚህ ክፉ ተግባራቸው ተሰውረው የነበሩ እነዚህ ወንጀለኞችን  ፖሊስ ከተሸሸጉበት ይዟቸው በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል።

አቃቢ ህግ ከዚህ በመነሳት በከባድ የውንብድና ወንጀል ክስ በመመስረት ፥ መዝገቡን ሲመረምር የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ የወንጀል ችሎት ክሳቸው ከተቋረጠባቸው አንዳረጌ ጥላሁንና 5ኛ ተከሳሽ መርጊያ ሽመልስ ውጪ ሌሎቹን በእስራት ቀጥቷቸዋል።

በዚህ መሰረት በተደራራቢ ክሶች የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበት የነበረው 2ኛው ተከሳሽ ፍስሃ ሻረው ተደማምሮበት በ30 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል።

ይህ ተከሳሽ ምንም እንኳን ከፍተኛ የወንጀል ተሳትፎ ቢኖረውም በአካል ተገኝቶ ክርክር አድርጎ የቅጣት ማቅለያ ባለማቅረቡ ነው የ30 ዓመት ፅኑ እስራት የተላለፈበት።

ፍርድ ቤቱ በግብር አባሮቹ ኢመኑ አዳነና መለሰ ሞገስ ላይም በእያንዳንዳቸው ላይ የ9 ዓመት ጽኑ እስራት ቅጣት አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ ፥ በሌለበት ውሳኔ በተሰጠው 2ኛ ተከሳሽ ፍስሃ ሻረውም የፌደራል ፖሊስ አፈላልጎ የእስራት ቅጣቱን እንዲፈፀም አዟል።

Abyssinia Law | Making Law Accessible! By Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Last Updated: 11 October 2022
Hits: 39679
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
Abyssinia Law | Making Law Accessible!
  • Prev
  • Next
Copyright © 2023 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Law Office